ጳጉሜ 2 የሪፎርም ቀንን አስመልክቶ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት ኩሪባቸው ታንቱ በሰጡት ማብራሪያ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባገባደድነው 2016 ዓ.ም ሁሉንም የሴት አደረጃጀቶች ሪፎርም በማድረግ የተሻለ ውጤት የተመዘገገበት ነው ብለዋል።
በተደረገው ሪፎርም ከ1ሺህ በላይ የቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበራትንና 40 ሺህ 4መቶ 75 በኩታ ገጠም 30 አባላትን የያዙ የሴቶች ልማት ህብረቶችን ማደራጀት መቻሉን ገልጸዋል።
ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸውን የሴት አደረጃጀቶች ከመፍጠር ጎን ለጎን በትምህርት፣በጤናና በሌሎችም ማህበራዊ ዘርፎች ሴቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ወ/ሪት ኩሪባቸው ገልጸዋል።
ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በዋናነት በሴት ልጅ ግርዛትና ያለ እድሜ ጋብቻን ቀድሞ ከመከላከል እና ጥቃቱን የፈጸሙ አካላትን ለህግ አቅርቦ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ከማድረግ ረገድ ይበል የሚያሰኝ ለውጥ መታየቱንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ:- አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ