ጳጉሜ 2 የሪፎርም ቀንን አስመልክቶ የቢሮው ምክትል ኃላፊና የሴቶች ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪት ኩሪባቸው ታንቱ በሰጡት ማብራሪያ የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ባገባደድነው 2016 ዓ.ም ሁሉንም የሴት አደረጃጀቶች ሪፎርም በማድረግ የተሻለ ውጤት የተመዘገገበት ነው ብለዋል።
በተደረገው ሪፎርም ከ1ሺህ በላይ የቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበራትንና 40 ሺህ 4መቶ 75 በኩታ ገጠም 30 አባላትን የያዙ የሴቶች ልማት ህብረቶችን ማደራጀት መቻሉን ገልጸዋል።
ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸውን የሴት አደረጃጀቶች ከመፍጠር ጎን ለጎን በትምህርት፣በጤናና በሌሎችም ማህበራዊ ዘርፎች ሴቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ወ/ሪት ኩሪባቸው ገልጸዋል።
ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች በዋናነት በሴት ልጅ ግርዛትና ያለ እድሜ ጋብቻን ቀድሞ ከመከላከል እና ጥቃቱን የፈጸሙ አካላትን ለህግ አቅርቦ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ከማድረግ ረገድ ይበል የሚያሰኝ ለውጥ መታየቱንም ተናግረዋል።
ዘጋቢ:- አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን ዛላ ወረዳ ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ
በሀድያ ዞን ሌሞ ወረዳ ከ5 ሺህ 9 መቶ በላይ ተማሪዎች ክልላዊና ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ
”ከተረጅነት ወደ ምርታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው