የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የክልሉን ህዝብ በማስተባበር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡
በክልሉ ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ረገድ እየሰራ ያለው ተግባር የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን አብራተዋል፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በበኩላቸው በክልሉ ያሉ የመልማት አቅሞችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም የተጀመሩ ለውጦችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም በመተግበር የተገኙ ውጤቶች፣ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ የውይይት ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ዘጋቢ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ