የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የክልሉን ህዝብ በማስተባበር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡
በክልሉ ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ረገድ እየሰራ ያለው ተግባር የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን አብራተዋል፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በበኩላቸው በክልሉ ያሉ የመልማት አቅሞችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም የተጀመሩ ለውጦችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም በመተግበር የተገኙ ውጤቶች፣ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ የውይይት ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ዘጋቢ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ