የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የክልሉን ህዝብ በማስተባበር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡
በክልሉ ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ረገድ እየሰራ ያለው ተግባር የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን አብራተዋል፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በበኩላቸው በክልሉ ያሉ የመልማት አቅሞችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም የተጀመሩ ለውጦችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም በመተግበር የተገኙ ውጤቶች፣ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ የውይይት ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ዘጋቢ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ