የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ክልሉ ከተመሠረተ ወዲህ የክልሉን ህዝብ በማስተባበር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው፡፡
በክልሉ ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ከማጠናቀቅ ረገድ እየሰራ ያለው ተግባር የህዝብ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን አብራተዋል፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በበኩላቸው በክልሉ ያሉ የመልማት አቅሞችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን በአግባቡ መጠቀም የተጀመሩ ለውጦችን ማስቀጠል ይገባል ብለዋል፡፡
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም በመተግበር የተገኙ ውጤቶች፣ ተግዳሮቶች እና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በክልሉ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ የውይይት ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ዘጋቢ: አንዱዓለም ኡማ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተጀመረ
የተቀናጀ የመሬት አጠቃቀም ዕቅድ ያረጁ ቡናዎችን ለማደስና አዲስ ተከላን ለማስፋፋት ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
የስራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም የሚያሳድግ የ12.8 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ