ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የኬሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዮሐንስ ኃይሉ፤ የመሻገር ውጤቶች እየታዩ እንደሆነ በመግለጽ ከንግግር ባለፈ ሁሉም በተግባር በርትቶ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
በኮሬ ዞን የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ጢሞቲዎስ በቀለ ያለን የተፈጥሮ ፀጋና ቀደምት አባቶች በጣሉልን መሠረት ላይ ቆመን ወቅቱን በመገንዘብ በጋራ በመተባበር ከተማን ማሻገርና አገርን ማሳደግ እንችላለን በማለት ተናግረዋል።
የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ውይይቱ 5ኛ ዙር የህዳሴ ግድብ ውኃ ሙሌት በተካሄደበት ማግሥት መሆኑ የተለየ እንደሚያደርገው በመግለጽ በሠላም ጊዜ ሠላም በመሥራት ከሰው ሠራሽ አደጋ ራሳችንን በመጠበቅ እየታየ ያለውን ብሩህ ተስፋ ከዳር እናደርሳለን ብለዋል።
ከተሳታፊዎች አቶ ምትኩ ኩራዝ፣ መምህር አርጋው ጥላሁንና ሌሎች በሰጡት አስተያየት በበርካታ ችግሮች መካከል በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን በማንሳት ያለንን በመንከባከብ፣ ቀሪውን በብርታት መሥራት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
አክለውም ልማት፣ ሠላምና ማህበራዊ ጉዳዮች ለተወሰኑ አካላት የሚተው ባለመሆናቸው በአንድነትና በብርታት መሥራት እንደሚጠይቅ አስታውሰዋል።
በፓናል ውይይቱ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እና የመንግሥት ሠራተኞች ተሳተፈዋል።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ