ሀዋሳ፡ ጳጉሜ 01/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) “የመሻገር ጥሪቶች፤ የአዲስ ብርሃን ወረቶች” በሚል መሪ ቃል የጋሞ ዞን፣ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና በአርባ ምንጭ ማዕከል የሚገኙ የክልል ቢሮዎች የመሻገር ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል።
የጋሞ ዞን ዋና የመንግሥት ተጠሪ አቶ ሰብስቤ እየተመዘገቡ ያሉ ለውጦችን ለማስቀጠል በአዲሱ አመት አዲስ ተስፋ ሰንቀን መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የክልሉ የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ገብረመስቀል ጫላ፤ የ2016 ዓ.ም የክልሉ ሕዝቦች ራስን በራስ ለማስተዳደር በፍላጎታቸው የመደራጀት ይሁንታ ያገኙበት፣ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች እና ሌሎች የልማት ትሩፋቶች የተመዘገቡበት ዓመት እንደሆነ አስታውሰው በመጪው ዓመት ለልማት የተነቃቃውን የክልሉን ሕዝብ ይዘን ከሠራን ሰፊ የመልማት ዕድል በእጃችን አለ በማለት ተናግረዋል።
በተሠማራንበት መስክ ሁሉ ለአገር ግንባታ ተስፋ ሰንቀን በትጋት መሥራት ይጠበቅብናል ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የምንቀበለው አዲሱ ዓመት የተስፋ ብርሃን የምንሰንቅበት እንዲሆንም ተመኝተዋል።
በመሻገር ቀን የአርባ ምንጭ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የሥራ እንቅስቃሴ እና ሌሎች የልማት ድርጅቶች በተሣታፊዎች ተጎብኝተዋል።
ዘጋቢ: ወ/ገብርኤል ላቀው – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ