በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 29ኛ መደበኛ ጉባኤው እያካሄደ ነው፡፡
የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፈትለወርቅ በቀለ በጉባኤው መክፈቻ ንግግራቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በርካታ የመሠረተ ልማት፣ የጌጠኛው ድንጋይ ንጣፍ፣ የአዳዲስ መንገድ ከፈታና በርካታ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ጥረት የተደረገበት ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
አመራሩ ከህዝብ የሚነሱ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአግባቡ በማድመጥና ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ለዘላቂ ልማት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
ጉባኤው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላትን ጨምሮ የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ