በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 29ኛ መደበኛ ጉባኤው እያካሄደ ነው፡፡
የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፈትለወርቅ በቀለ በጉባኤው መክፈቻ ንግግራቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በርካታ የመሠረተ ልማት፣ የጌጠኛው ድንጋይ ንጣፍ፣ የአዳዲስ መንገድ ከፈታና በርካታ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ጥረት የተደረገበት ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
አመራሩ ከህዝብ የሚነሱ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአግባቡ በማድመጥና ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ለዘላቂ ልማት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
ጉባኤው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላትን ጨምሮ የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ