በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 29ኛ መደበኛ ጉባኤው እያካሄደ ነው፡፡
የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፈትለወርቅ በቀለ በጉባኤው መክፈቻ ንግግራቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በርካታ የመሠረተ ልማት፣ የጌጠኛው ድንጋይ ንጣፍ፣ የአዳዲስ መንገድ ከፈታና በርካታ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ጥረት የተደረገበት ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
አመራሩ ከህዝብ የሚነሱ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአግባቡ በማድመጥና ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ለዘላቂ ልማት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
ጉባኤው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላትን ጨምሮ የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና አርባምንጭ ከተማን በመርታት ወደ አሸናፊነት ተመለሰ
በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት በመሳተፍ የሚፈልገውን መንግስት ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት ተገለጸ
ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው – አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል