በጌዴኦ ዞን የዲላ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 4ኛ ዙር 29ኛ መደበኛ ጉባኤው እያካሄደ ነው፡፡
የከተማው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ወ/ሮ ፈትለወርቅ በቀለ በጉባኤው መክፈቻ ንግግራቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በርካታ የመሠረተ ልማት፣ የጌጠኛው ድንጋይ ንጣፍ፣ የአዳዲስ መንገድ ከፈታና በርካታ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ ጥረት የተደረገበት ዓመት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
አመራሩ ከህዝብ የሚነሱ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአግባቡ በማድመጥና ተገቢውን ምላሽ በመስጠት ለዘላቂ ልማት በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
ጉባኤው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን በጉባኤው የምክር ቤቱ አባላትን ጨምሮ የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሞዴል የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሟላትና ምቹ የመማሪያ ከባቢን ለልጆች መፍጠር ለቀጣዩ የትምህርት ደረጃዎች መሠረት መሆኑ ተገለጸ
በጎፋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ጥራትና ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታወቀ