ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ከተማ አስተዳደር ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ኘሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል፡፡
ግንባታቸው ተጠናቀው ለአገልግሎት ከበቁ ፕሮጀክቶች መካከል የዲች፣ በኦዳያአ ቀበሌ የተገነባው ድልድይ፣ ለኢንቨስትመንት ተነሺዎች በሁለት ሳይት የተገነቡ 30 የመኖሪያ ቤቶች ተጠቃሾች መሆናቸውን የከተማው ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሽፈራው አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ስብራት ለመጠገን ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችንና ባለ አንድ ወለል ቤተ መጽሐፍት በመገንባት የትምህርትን ጥራት ለማሻሻል የሚያግዙ ኘሮጀክቶችም መመረቃቸውን ከንቲባው ተናግረዋል።
ለኘሮጀክቶቹ ከ1 መቶ 10 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል ተብሏል፡፡
በምረቃው የተገኙ የዲላ ከተማ ምክር ቤት አባላት በከተማው እየተከናወኑ ያሉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በመጎብኘት በከተማው የሚበረታታ የልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፦ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ