ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በዲላ ከተማ አስተዳደር ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ኘሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል፡፡
ግንባታቸው ተጠናቀው ለአገልግሎት ከበቁ ፕሮጀክቶች መካከል የዲች፣ በኦዳያአ ቀበሌ የተገነባው ድልድይ፣ ለኢንቨስትመንት ተነሺዎች በሁለት ሳይት የተገነቡ 30 የመኖሪያ ቤቶች ተጠቃሾች መሆናቸውን የከተማው ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሽፈራው አስታውቀዋል፡፡
የትምህርት ስብራት ለመጠገን ተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎችንና ባለ አንድ ወለል ቤተ መጽሐፍት በመገንባት የትምህርትን ጥራት ለማሻሻል የሚያግዙ ኘሮጀክቶችም መመረቃቸውን ከንቲባው ተናግረዋል።
ለኘሮጀክቶቹ ከ1 መቶ 10 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል ተብሏል፡፡
በምረቃው የተገኙ የዲላ ከተማ ምክር ቤት አባላት በከተማው እየተከናወኑ ያሉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በመጎብኘት በከተማው የሚበረታታ የልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ፦ እምነት ሽፈራው- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ