ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የከተማውን ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ችግርን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን በጌዴኦ ዞን የገደብ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
በከተማው ከ1 መቶ 20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተሠራ ያለው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 91 በመቶ መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡
የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ የከተማው ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ጥያቄ ሲያነሳ መቆየቱን አንስተው ችግሩን ለመቅረፍ ከ1 መቶ 20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተሠራ የሚገኘው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 91 ከመቶ ተጠናቆ በከፊል አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡
የገደብ ከተማ አስተዳደር ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ደመቀ፤ ከአበዳሪ ተቋም እና በማችንግ ፈንድ በጀት እየተሠራ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ከ57 ሺህ በላይ የሚሆነውን የከተማውን የህብረተሰብ ክፍል የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ፍቃዱ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ወደመጠናቀቂያው ምዕራፍ መሸጋገሩን አንስተው የተሠሩ አዳዲስ የውሃ መተላለፊያ መሥመሮችን ከነባሮቹ ጋር በማገናኘት ህብረተሰቡ ሙሉ በሙሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ