ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የከተማውን ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ችግርን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን በጌዴኦ ዞን የገደብ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
በከተማው ከ1 መቶ 20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተሠራ ያለው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 91 በመቶ መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡
የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታሪኩ ሮቤ የከተማው ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ጥያቄ ሲያነሳ መቆየቱን አንስተው ችግሩን ለመቅረፍ ከ1 መቶ 20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተሠራ የሚገኘው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት 91 ከመቶ ተጠናቆ በከፊል አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡
የገደብ ከተማ አስተዳደር ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ደመቀ፤ ከአበዳሪ ተቋም እና በማችንግ ፈንድ በጀት እየተሠራ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ከ57 ሺህ በላይ የሚሆነውን የከተማውን የህብረተሰብ ክፍል የንፁህ መጠጥ ውሃ አገልግሎት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ፍቃዱ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ወደመጠናቀቂያው ምዕራፍ መሸጋገሩን አንስተው የተሠሩ አዳዲስ የውሃ መተላለፊያ መሥመሮችን ከነባሮቹ ጋር በማገናኘት ህብረተሰቡ ሙሉ በሙሉ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ዘጋቢ: ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ