በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የኮሬ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈጉባዔ ወ/ሮ አካላት በቀለ ከህብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎች በመቀበል ተገቢ ምላሽ ሊያገኝ እንዲያገኝ መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡
በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኮሬ ዞን ተወካይ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) የኮሬ ዞን ከህብረተሰቡ ለሚነሱት ጥያቄዎች ባለቤት መድቦ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል።
የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ምቹ መሠረተ ልማት እንዲኖር ህዝቡ የሚያነሳው ጥያቄ ተገቢነት ያለው መሆኑን በመግለጽ በወረዳና በዞን የሚፈቱ ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየፈታን ከአቅማችን በላይ የሆነውን ለፌደራል መንግሥት እናቀርባለን ብለዋል።
የኮሬ ዞን ምክትል ኃላፊ፣ የግብርና መምሪያና የመሠረተ ልማትና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ አቶ አስታረቀኝ አንደባ ፣ የግብአት እጥረት በአገር ደረጃ የገጠመ መሆኑን ገልጸው መስኖ ማዘመን የህልውና ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል።
በኮሬ ዞን የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ጢሞቴዎስ በቀለ ተጀምሮ ያልተጠናቀቁ ፕሮጀክቶች ላይ ህብረተሰቡ ለሚያነሳው ጥያቄ ተቀናጅተን መሥራት ይጠበቅብናል ብለዋል።
ዘጋቢ: ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
በ17 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሞሪንጋ ጂን ባንክ ለማቋቋም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ