ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀገራዊ ምክክር ሂደት የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሀገሪቱ ሠላም ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ እንደመሆኑ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ የድርሻችንን ልንወጣ ዝግጁ ነን ብለዋል።
ኮሚሽኑ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በእኩል በማሳተፍ ሀገር የሁሉም መሆኗን ያመላከተበት ነው ያሉት ተሳታፊዎቹ ያለህብረተሰብ ተሳትፎ ዘላቂ ሠላምን ማረጋገጥ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበንበታል ብለዋል።
አለመግባባትን በምክክር ለመፍታት መመካከራችን ሁነኛ መፍትሔ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ- ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
የሆሳዕና እናት ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ከአንድ መቶ በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካሞች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች