ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀገራዊ ምክክር ሂደት የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሀገሪቱ ሠላም ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ እንደመሆኑ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ የድርሻችንን ልንወጣ ዝግጁ ነን ብለዋል።
ኮሚሽኑ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በእኩል በማሳተፍ ሀገር የሁሉም መሆኗን ያመላከተበት ነው ያሉት ተሳታፊዎቹ ያለህብረተሰብ ተሳትፎ ዘላቂ ሠላምን ማረጋገጥ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበንበታል ብለዋል።
አለመግባባትን በምክክር ለመፍታት መመካከራችን ሁነኛ መፍትሔ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ- ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
በ17 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሞሪንጋ ጂን ባንክ ለማቋቋም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ