ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀገራዊ ምክክር ሂደት የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሀገሪቱ ሠላም ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ እንደመሆኑ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ የድርሻችንን ልንወጣ ዝግጁ ነን ብለዋል።
ኮሚሽኑ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በእኩል በማሳተፍ ሀገር የሁሉም መሆኗን ያመላከተበት ነው ያሉት ተሳታፊዎቹ ያለህብረተሰብ ተሳትፎ ዘላቂ ሠላምን ማረጋገጥ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበንበታል ብለዋል።
አለመግባባትን በምክክር ለመፍታት መመካከራችን ሁነኛ መፍትሔ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ- ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ