ሀዋሳ፡ ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሀገራዊ ምክክር ሂደት የድርሻቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን በምክክሩ እየተሳተፉ የሚገኙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰብ ክፍሎች ተናገሩ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ በምክክር ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሀገሪቱ ሠላም ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ እንደመሆኑ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ የድርሻችንን ልንወጣ ዝግጁ ነን ብለዋል።
ኮሚሽኑ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በእኩል በማሳተፍ ሀገር የሁሉም መሆኗን ያመላከተበት ነው ያሉት ተሳታፊዎቹ ያለህብረተሰብ ተሳትፎ ዘላቂ ሠላምን ማረጋገጥ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበንበታል ብለዋል።
አለመግባባትን በምክክር ለመፍታት መመካከራችን ሁነኛ መፍትሔ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ዘጋቢ: አማኑኤል አጤቦ- ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ