የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ እየተሳተፉ ያሉ ወጣቶች መካከል ወጣት ሮዛ ሸምሱ፣ ታምራት ይልማ እና ማርታ ገብሩ ምክክሩ የሚገጥሙ ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ መልካም አጋጠሚ የፈጠረ ነው ብለዋል::
ወጣቶቹ ለሃገር የመፍትሄ ሐሳብ እንዲያመጡ እድለ የፈጠረ ውይይት መሆኑን ወጣቶቹ አመላክተዋል::
ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት በሰከነ መንፈስ፣ በእውነት እና በእውቀት ላይ ተመስርተው ወጣቶች መመካከር እንዳለባቸውም ወጣቶቹ መክረዋል::
በሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት የሚከሰቱ ግጭቶች ወጣቶችን እየቀጠፉ ስለነበር ምክክሩ ወጣቶች ያላቸውን ተስፋ እንዲያለመልሙ ያስቻለ እንደሆነም አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች ጠቁመዋል::
ዘጋቢ: በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ