የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ እየተሳተፉ ያሉ ወጣቶች መካከል ወጣት ሮዛ ሸምሱ፣ ታምራት ይልማ እና ማርታ ገብሩ ምክክሩ የሚገጥሙ ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ መልካም አጋጠሚ የፈጠረ ነው ብለዋል::
ወጣቶቹ ለሃገር የመፍትሄ ሐሳብ እንዲያመጡ እድለ የፈጠረ ውይይት መሆኑን ወጣቶቹ አመላክተዋል::
ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመፍታት በሰከነ መንፈስ፣ በእውነት እና በእውቀት ላይ ተመስርተው ወጣቶች መመካከር እንዳለባቸውም ወጣቶቹ መክረዋል::
በሀገራችን በተለያዩ ጊዜያት የሚከሰቱ ግጭቶች ወጣቶችን እየቀጠፉ ስለነበር ምክክሩ ወጣቶች ያላቸውን ተስፋ እንዲያለመልሙ ያስቻለ እንደሆነም አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች ጠቁመዋል::
ዘጋቢ: በየነ ሰላሙ – ከሆሳዕና ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ