በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሁለት ዞኖች ከ19 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ከ274 ሚሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ የሃይላንድስ ሪዚሊያንስ አክቲቪቲ ፕሮጀክት በይፋ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል።
በመክፈቻ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጋንታ ጋምአ እንደ ክልል በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ፕርጀክቱ አጋዥ በመሆኑ ለፕሮጀክቱ ሰኬታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት መረባረብ አለባቸው ብለዋል።
በአሜሪካ መንግሥት ተራድኦ ድርጅት የሚደገፈው የሃይላንድ አክቲቪቲ ከገበያ ተዋናይ አካላት ጋር በመሥራት በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የታቀፉ ቤተሰቦች የተሻለ ምርታማ እንዲሆኑ፣ አማራጭ የገቢ ምንጭ እንዲያገኙ፣ የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲሳተፉና የሥራ ዕድል እንዲያገኙ እንደሚያግዝ የአሜሪካ መንግሥት ተራድኦ ድርጅት የኢትዮጵያ ተወካይ ዶ/ር ልዑልሰገድ በላይ ተናግረዋል።
የፕሮግራሙ ዋና ግብ በሀገር ደረጃ በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የታቀፉ 120 ሺህ ቤተሰቦች በምግብ ራሳቸውን ችለው በዘላቂነት ከተረጂነት ተላቀው ከፕሮግራሙ መውጣት እንዲችሉ ማገዝ ነው ያሉት ደግሞ የሃይላንድ አክቲቪቲ ሪዚሊያንስ ፕሮጀክት ምክትል አስተባባሪ አቶ ጥላሁን አስማረ፤ ፕሮግራሙ በደቡብ ኢትዮጵያ 5 ወረዳዎች ተግባራዊ እንደሚሆን ገልፀዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 19 ሺህ 487 ዜጎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግና ከ274 ሚሊዮን 529 ሺህ ብር በላይ እንደሚፈጅ የደቡብ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አስተባባሪ ወ/ሮ ስምረት ሲማኖ ተናግረዋል።
በፕሮጀክቱ መክፈቻ ፕሮግራም ላይ የፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን የገበያ ተዋናይ አካላትም በምግብ ራስን ለመቻልና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገው እንቅስቃሴ ቀርቧል።
ዘጋቢ፡ አማሮ አርሳባ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ