እርቀ ሰላም “ለአንድነት፤ ለአብሮነትና ለወንድማማችነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ነው::
የሰላም እጦቱን ወደነበረበት ሰላም ለመመለስ የከተማዉ ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል።
በሰላም ኮንፈረንሱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሼህ መሀመድ ከሊል፣ የሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት አስተዳዳሪ መልዓከ ህይወት ቀሲስ ንጉሴ ባወቀን ጨምሮ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የወረዳ አመራሮች፣ የአጎራባች ወረዳዎች፣ የከተማው ነዋሪዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ናስር ጀማል – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ