እርቀ ሰላም “ለአንድነት፤ ለአብሮነትና ለወንድማማችነት” በሚል መሪ ሃሳብ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ቅበት ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ነው::
የሰላም እጦቱን ወደነበረበት ሰላም ለመመለስ የከተማዉ ህዝብ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሟል።
በሰላም ኮንፈረንሱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የእስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንት ሼህ መሀመድ ከሊል፣ የሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት አስተዳዳሪ መልዓከ ህይወት ቀሲስ ንጉሴ ባወቀን ጨምሮ የዞንና የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የወረዳ አመራሮች፣ የአጎራባች ወረዳዎች፣ የከተማው ነዋሪዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ: ናስር ጀማል – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና አርባምንጭ ከተማን በመርታት ወደ አሸናፊነት ተመለሰ
በ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በንቃት በመሳተፍ የሚፈልገውን መንግስት ለመምረጥ መዘጋጀት እንዳለበት ተገለጸ
ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ ነው – አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤል