ሀዋሳ፡ ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአሪ ዞን ከገሊላ ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ “ተስፋ ያለው ባለራዕይ በጎ አድራጎት ማህበር” አባላት በደቡብ ኣሪ ወረዳ የከተማ ፅዳትና ችግኝ ተከላ አከናውነዋል ፡፡
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግዛው ኃይሌ ማህበሩ ላደረገው በጎፈቃድ አገልግሎት ምስጋና አቅርበዋል ፡፡
በኣሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ሊግ ኃላፊ አቶ ናትናኤል ኤልያስ ተስፋ ያለው ባለራዕይ በጎ አድራጎት ማህበር እያከናወነ ያለው ተግባር የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር በመሆኑ ሊበረታታ ይገባል ብለዋል፡፡
ማህበሩ ሕጋዊ ዕውቅናን ካገኘ በኀላ የወጣቱን ግንኙነት በማሳለጥና የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለማቃለል እየሠራ መቆየቱን የማህበሩ አስተባባሪ ወጣት መርደክዮስ ዮሐንስ ገልፀዋል፡፡
በበጎ አገልግሎቱ ከተሳተፋ የማህበሩ አባላት መካከል ወጣት ተስፋዬ ተክሌና ውድዬ እሳቱ በጋራ እንደገለፁት የኢትዮጵያን ከፍታ ለማረጋጥ በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረው በነበራቸው ቆይታ መልካም ተሞክሮዎችን መለዋወጣቸውን አስረድተዋል ፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ- ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
በ17 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሞሪንጋ ጂን ባንክ ለማቋቋም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ