ሀዋሳ፡ ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በአሪ ዞን ከገሊላ ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ “ተስፋ ያለው ባለራዕይ በጎ አድራጎት ማህበር” አባላት በደቡብ ኣሪ ወረዳ የከተማ ፅዳትና ችግኝ ተከላ አከናውነዋል ፡፡
የደቡብ ኣሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግዛው ኃይሌ ማህበሩ ላደረገው በጎፈቃድ አገልግሎት ምስጋና አቅርበዋል ፡፡
በኣሪ ዞን የገሊላ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ሊግ ኃላፊ አቶ ናትናኤል ኤልያስ ተስፋ ያለው ባለራዕይ በጎ አድራጎት ማህበር እያከናወነ ያለው ተግባር የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር በመሆኑ ሊበረታታ ይገባል ብለዋል፡፡
ማህበሩ ሕጋዊ ዕውቅናን ካገኘ በኀላ የወጣቱን ግንኙነት በማሳለጥና የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለማቃለል እየሠራ መቆየቱን የማህበሩ አስተባባሪ ወጣት መርደክዮስ ዮሐንስ ገልፀዋል፡፡
በበጎ አገልግሎቱ ከተሳተፋ የማህበሩ አባላት መካከል ወጣት ተስፋዬ ተክሌና ውድዬ እሳቱ በጋራ እንደገለፁት የኢትዮጵያን ከፍታ ለማረጋጥ በሙሉ አቅማቸው አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረው በነበራቸው ቆይታ መልካም ተሞክሮዎችን መለዋወጣቸውን አስረድተዋል ፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ- ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ