ሀዋሳ፡ ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም (ደረቴድ) ኮሌጁ ከ40 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባውን የመረጃ ማዕከልና ለ27ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 561 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
የሆሳዕና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ምክትል ዲንና የመማር ማስተማር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ድንቁ ዳንኤል አለም አቀፋዊ የመረጃ ልውውጥ በማድረግ የትምህርት ጥራትን ወደ ተሻለ ደረጀ ለማሳደግ የመረጃ ማዕከሉ ግንባታ ያለው ፋይደ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሌጁ በመማር ማስተማር፣ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት የሚያከናውናቸውን ተግባራት ለማሳለጥ ማዕከሉ አጋዥ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ኮሌጁ በዕለቱ በመጀመሪያ ድግሪ 141 ሰልጣኞችንና ለመጀማሪያ ጊዜ በድፕሎማ የትምህርት መርሀ ግብሮች 420 በድምሩ 561 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡
በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተደድር እና የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እና ሌሎች የክልልና የዞን አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
ዘጋቢ:-ሳሙኤል መንታሞ- ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በማጠናከር ክልላዊ አንድነትን ማጎልበት እንደሚገባ ተገለጸ
ህዝበ ሙስሊሙ የመውሊድ በዓልን ሲያከብር በብዝሃነት ውስጥ የሚንፀባረቁ የመረዳዳትና የአብሮነት በጎ እሴቶችን ይበልጥ በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ