ሀዋሳ፡ ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ከወከሉ ተመራጮች አጀንዳን ለማሰባሰብ ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ ብሔራዊ ምክክር ዓላማው ብሔራዊ እርቅን ማምጣት መሆኑን ጠቁመው ተሳታፊዎች ውይይቱ እስከሚያልቅ በንቃት በመሳተፍ የሀገራዊ ምክክሩን ዓላማ በማሳካታ የሀገሪቱን ዘላቂ ሠላም ለማረጋገጥ በሚደረጉ ጥረቶች የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በውይይት መድረኩ በክልሉ ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ማለትም ከሃይማኖት ተቋማት፣ሲቪክ ማህበራት፣ከንግዱ ማህበረሰብ፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ወጣቶች፣ሴቶች፣አካል ጉዳተኞች፣የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ቋሚ ኮማቴ አባላትን ጨምሮ ከሶስቱም የመንግስት አካላት የተውጣጡና ሌሎችም አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።
ከውይይት መድረኩ ለአጠቃላይ ሀገራዊ ምክክር የሚሆኑ ወሳኝ ግብዓቶች ይገኙበታል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ:አማኑኤል አጤቦ- ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ