በምክር ቤቱ የ2016 አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ የቀረበ ሲሆን በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት እና ዕቅድ ዙሪያ ምክር ቤቱ አስተያየት በመስጠት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።
እየተካሄደ ባለው የሽግግር ምክርቤት መደበኛ ጉባኤ በዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ለእይታ ቀርቦ አስተያየት ተሰጥቶበታል።
የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው የዞኑ አስተዳደር ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት ማጠቃለያ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።
ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችንና የ2017 ረቂቅ በጀት ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።
ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን

More Stories
የሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በስፖርትና ባህል ልማት ዘርፍ የሚገኘውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አበክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ
ህግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ፍትህ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ሥራ አፈፃፀም አደመጠ
ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሠራ የዲላ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ