የባስኬቶ ዞን ሽግግር ምክርቤት 4ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ተካሄደ

በምክር ቤቱ የ2016 አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ የቀረበ ሲሆን በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት እና ዕቅድ ዙሪያ ምክር ቤቱ አስተያየት በመስጠት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

እየተካሄደ ባለው የሽግግር ምክርቤት መደበኛ ጉባኤ በዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የተዘጋጀ ዶክመንተሪ ፊልም ለእይታ ቀርቦ አስተያየት ተሰጥቶበታል።

የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ፍሬው ፍሻለው የዞኑ አስተዳደር ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት ማጠቃለያ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በሙሉ ድምፅ ጸድቋል።

ምክር ቤቱ የተለያዩ ሹመቶችንና የ2017 ረቂቅ በጀት ተወያይቶ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ዘጋቢ: አወል ከድር – ከሳውላ ጣቢያችን