የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ወለቱ ዋዮ መድረኩን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ከዚህ ቀደም ከህብረተሰቡ ሲነሱ የቆዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የሰላም እጦት፣ የመልማት ጥያቄዎችና ሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮች ደረጃ በጀረጃ ቀርበው ምላሽ ይሰጥባቸዋል ነው ያሉት፡፡
በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቡርጂ ህዝብ ተወካይ አቶ ከድር መሐመድ ከህብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን በመውሰድ ጥያቄዎቹ በሚፈቱበት አግባብ በየደረጃው ለሚገኙ ባለድርሻዎች ይቀርባሉ ብለዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የቡርጂ ዞን ተወካይ አቶ ማሬ አልማየሁ በውይይት መድረኩ በሁለም ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በመገምገም ለሚመለከታቸው አካላት ለማቅረብ የህዝቡ ውይይት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አደን ማዶና ደስታ እማሌ በሰጡት አስተያየት በዞን ደረጃ የሚስተዋለው የሰላም ጉዳይ፣ የመንገድ፣ የመብራት፣ የኔትወርክና የውሃ ችግሮች ሁሌም ከህብረተሰቡ የሚነሱና እልባት ያላገኙ እንደሆነ በማንሳት የህዝብ ተወካዮችም ችግሮችን ለመፍታት እንዲሠሩ ጠይቀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዮሴፍ ቶልኬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ