የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ወለቱ ዋዮ መድረኩን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ከዚህ ቀደም ከህብረተሰቡ ሲነሱ የቆዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የሰላም እጦት፣ የመልማት ጥያቄዎችና ሌሎችም ተያያዥ ጉዳዮች ደረጃ በጀረጃ ቀርበው ምላሽ ይሰጥባቸዋል ነው ያሉት፡፡
በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቡርጂ ህዝብ ተወካይ አቶ ከድር መሐመድ ከህብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን በመውሰድ ጥያቄዎቹ በሚፈቱበት አግባብ በየደረጃው ለሚገኙ ባለድርሻዎች ይቀርባሉ ብለዋል፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የቡርጂ ዞን ተወካይ አቶ ማሬ አልማየሁ በውይይት መድረኩ በሁለም ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በመገምገም ለሚመለከታቸው አካላት ለማቅረብ የህዝቡ ውይይት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል አቶ አደን ማዶና ደስታ እማሌ በሰጡት አስተያየት በዞን ደረጃ የሚስተዋለው የሰላም ጉዳይ፣ የመንገድ፣ የመብራት፣ የኔትወርክና የውሃ ችግሮች ሁሌም ከህብረተሰቡ የሚነሱና እልባት ያላገኙ እንደሆነ በማንሳት የህዝብ ተወካዮችም ችግሮችን ለመፍታት እንዲሠሩ ጠይቀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ዮሴፍ ቶልኬ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ