ሀዋሳ፡ ነሐሴ 13/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት አባላት በ18ኛ መደበኛ ስብሰባው ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ጋር የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ ግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት የተካሄደው 18ኛው የመስተዳድር ምክር ቤት ስብሰባ፥ የአንድ አመቱን ጉዞ ትውስታ ምን ይመስል እንደነበር ሰነድ ቀርቦ የአመቱን አፈጻጸም በማየት ተጀምሯል።
መስተዳድር ምክር ቤቱ የ2017 ዕቅድ ማጠቃለያ ላይ በዝርዝር የመከረ ሲሆን፥ በተለይ በዕቅድ ሊካተቱና ሊሻሻሉ ይገባቸዋል ብሎ ከዚህ ቀደም በዕቅድ ግምገማ ወቅት በሰጠው ግብረ መልስ መሠረት ማስተካከያ የተደረገበትን የ2017 ዕቅድ ማጠቃለያ የግብ ስምምነት በክልሉ የፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
ሴክተር መስሪያ ቤቶች በ2017 በጀት አመት ዕቅድ ዙሪያ የፈጻሚ ማዘጋጃ መድረክ በማካሄድ በተቋማት ዋና ዋና ግቦች ላይ ከፈጻሚዎቻቸው ጋር የጋራ መግባባት ላይ መድረስ እንደሚገባ ያሳሰቡት ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው፥ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ከባቢ መፍጠር እና ከመስሪያ ቤት ባለድርሻ አካላት ጋር መወያየት እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት አባላት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ግብ ስምምነት ከርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ጋር ተፈራርመዋል።
ዘጋቢ፡ ዘላለም ተስፋዬ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ