አስተያየታቸውን ከሰጡን የከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ማንደፍሮ ታንና አብነት እያሱ፤ ከዚህ ቀደም ሰለከተማ ግብርና እንደማያውቁና በመሸመት ብቻ ይተዳደሩ እንደነበር አሰታውሰው ዛሬ ላይ በጓሮአቸው ድንች፣ ጥቅል ጎመን፣ የደጋ በቆሎና ሌሎችንም በማምረት ከውጭ ሸምተው ከመጠቀም ተላቀው ወጪያቸውን መቀነስ መቻላቸውን ገልጸዋል።
በከተማ ግብርና መሳተፋቸው አሁን እየታየ ያለውን የኑሮ ጫና መቋቋም እንዳስቻላቸውም ጠቁመዋል።
የገሊላ ከተማ አስተዳደር ግብርና ዮኒት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ፤ ከተማው አርሶአደሩንም ከተማ ነዋሪውንም አቅፎ የያዘ እንደመሆኑ በከተማ ግብርና ምግባቸውን ከጓሮአቸው እንዲያገኙ በየጓሮአቸው ባለው ትንሽ መሬት የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን እንዲያለሙ ግንዛቤ በመስጠት እንዲያመርቱ እያስቻለ ሲሆን በዚህም አብዛኛዎቹ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ