አስተያየታቸውን ከሰጡን የከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ማንደፍሮ ታንና አብነት እያሱ፤ ከዚህ ቀደም ሰለከተማ ግብርና እንደማያውቁና በመሸመት ብቻ ይተዳደሩ እንደነበር አሰታውሰው ዛሬ ላይ በጓሮአቸው ድንች፣ ጥቅል ጎመን፣ የደጋ በቆሎና ሌሎችንም በማምረት ከውጭ ሸምተው ከመጠቀም ተላቀው ወጪያቸውን መቀነስ መቻላቸውን ገልጸዋል።
በከተማ ግብርና መሳተፋቸው አሁን እየታየ ያለውን የኑሮ ጫና መቋቋም እንዳስቻላቸውም ጠቁመዋል።
የገሊላ ከተማ አስተዳደር ግብርና ዮኒት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ፤ ከተማው አርሶአደሩንም ከተማ ነዋሪውንም አቅፎ የያዘ እንደመሆኑ በከተማ ግብርና ምግባቸውን ከጓሮአቸው እንዲያገኙ በየጓሮአቸው ባለው ትንሽ መሬት የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን እንዲያለሙ ግንዛቤ በመስጠት እንዲያመርቱ እያስቻለ ሲሆን በዚህም አብዛኛዎቹ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ