አስተያየታቸውን ከሰጡን የከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ማንደፍሮ ታንና አብነት እያሱ፤ ከዚህ ቀደም ሰለከተማ ግብርና እንደማያውቁና በመሸመት ብቻ ይተዳደሩ እንደነበር አሰታውሰው ዛሬ ላይ በጓሮአቸው ድንች፣ ጥቅል ጎመን፣ የደጋ በቆሎና ሌሎችንም በማምረት ከውጭ ሸምተው ከመጠቀም ተላቀው ወጪያቸውን መቀነስ መቻላቸውን ገልጸዋል።
በከተማ ግብርና መሳተፋቸው አሁን እየታየ ያለውን የኑሮ ጫና መቋቋም እንዳስቻላቸውም ጠቁመዋል።
የገሊላ ከተማ አስተዳደር ግብርና ዮኒት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ፤ ከተማው አርሶአደሩንም ከተማ ነዋሪውንም አቅፎ የያዘ እንደመሆኑ በከተማ ግብርና ምግባቸውን ከጓሮአቸው እንዲያገኙ በየጓሮአቸው ባለው ትንሽ መሬት የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን እንዲያለሙ ግንዛቤ በመስጠት እንዲያመርቱ እያስቻለ ሲሆን በዚህም አብዛኛዎቹ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ