አስተያየታቸውን ከሰጡን የከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ማንደፍሮ ታንና አብነት እያሱ፤ ከዚህ ቀደም ሰለከተማ ግብርና እንደማያውቁና በመሸመት ብቻ ይተዳደሩ እንደነበር አሰታውሰው ዛሬ ላይ በጓሮአቸው ድንች፣ ጥቅል ጎመን፣ የደጋ በቆሎና ሌሎችንም በማምረት ከውጭ ሸምተው ከመጠቀም ተላቀው ወጪያቸውን መቀነስ መቻላቸውን ገልጸዋል።
በከተማ ግብርና መሳተፋቸው አሁን እየታየ ያለውን የኑሮ ጫና መቋቋም እንዳስቻላቸውም ጠቁመዋል።
የገሊላ ከተማ አስተዳደር ግብርና ዮኒት ኃላፊ አቶ ተመስገን ተሾመ፤ ከተማው አርሶአደሩንም ከተማ ነዋሪውንም አቅፎ የያዘ እንደመሆኑ በከተማ ግብርና ምግባቸውን ከጓሮአቸው እንዲያገኙ በየጓሮአቸው ባለው ትንሽ መሬት የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችን እንዲያለሙ ግንዛቤ በመስጠት እንዲያመርቱ እያስቻለ ሲሆን በዚህም አብዛኛዎቹ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ዘጋቢ: ከተማ በየነ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ