ጉባኤዉ በሁለት ተከታታይ ቀናት ቆይታቸዉ የወረዳውን የ2016 በጀት ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትና የ2017 ዕቅድ፣የአስፈፃሚ መሰሪያ ቤቶች እና የፍርድ ቤት የዓመቱ አፈፃፀምና የ2017 ዕቅድ ተገምግሟል።
በወረዳው የ2016 በጀት አመት አስተዳደር ምክር ቤት አፈፃፀምና የ2017 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ለተነሱ ሐሳቦች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ አልጋጋ ባልንሴ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በብቃት ለመመለስ ገቢ አሰባሰብ ለይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።
ለአፈፃፀሙ ስከታማነትም የምክር ቤት አባላት ህብረተሰቡን የማስተባበር ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ምክር ቤቱ የ2017 በጀት አመት ሥራ ማስፈፀሚያ 2መቶ 69ሚሊዮን 1መቶ 27ሺህ 5መቶ 3 ብር ረቂቅ በጀት ቀርቦላቸዉ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።
የወረዳዉ ዋና አፈ ጉባኤና ምክትል አፈ ጉባኤን ጨምሮ ሌሎች በተጓደሉ ካቢኔ አባላትና ቋሚ ኮሚቴዎች ቦታ ሹመት ቀርቦ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል።
ዘጋቢ ፡ ገጶስ አየለ ከጂንካ ቅርንጫፍ!!!

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ