በደቡብ ኦሞ ዞን የማሌ ወረዳ ምክር ቤት 4ኛ ዙር፣5ኛ ዓመት 37ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካደ

ጉባኤዉ በሁለት ተከታታይ ቀናት ቆይታቸዉ የወረዳውን የ2016 በጀት ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትና የ2017 ዕቅድ፣የአስፈፃሚ መሰሪያ ቤቶች እና የፍርድ ቤት የዓመቱ አፈፃፀምና የ2017 ዕቅድ  ተገምግሟል።

በወረዳው የ2016 በጀት አመት አስተዳደር ምክር ቤት አፈፃፀምና የ2017 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ለተነሱ ሐሳቦች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ አልጋጋ ባልንሴ  የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በብቃት ለመመለስ  ገቢ  አሰባሰብ ለይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ለአፈፃፀሙ ስከታማነትም የምክር ቤት አባላት ህብረተሰቡን የማስተባበር ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

ምክር ቤቱ የ2017 በጀት አመት ሥራ ማስፈፀሚያ  2መቶ 69ሚሊዮን 1መቶ 27ሺህ 5መቶ 3 ብር ረቂቅ በጀት ቀርቦላቸዉ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

የወረዳዉ ዋና አፈ ጉባኤና ምክትል አፈ ጉባኤን ጨምሮ ሌሎች በተጓደሉ ካቢኔ አባላትና ቋሚ ኮሚቴዎች ቦታ ሹመት ቀርቦ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል።

ዘጋቢ ፡ ገጶስ አየለ ከጂንካ ቅርንጫፍ!!!