ጉባኤዉ በሁለት ተከታታይ ቀናት ቆይታቸዉ የወረዳውን የ2016 በጀት ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትና የ2017 ዕቅድ፣የአስፈፃሚ መሰሪያ ቤቶች እና የፍርድ ቤት የዓመቱ አፈፃፀምና የ2017 ዕቅድ ተገምግሟል።
በወረዳው የ2016 በጀት አመት አስተዳደር ምክር ቤት አፈፃፀምና የ2017 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ ላይ ለተነሱ ሐሳቦች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የማሌ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ አልጋጋ ባልንሴ የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በብቃት ለመመለስ ገቢ አሰባሰብ ለይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።
ለአፈፃፀሙ ስከታማነትም የምክር ቤት አባላት ህብረተሰቡን የማስተባበር ሚናውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
ምክር ቤቱ የ2017 በጀት አመት ሥራ ማስፈፀሚያ 2መቶ 69ሚሊዮን 1መቶ 27ሺህ 5መቶ 3 ብር ረቂቅ በጀት ቀርቦላቸዉ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።
የወረዳዉ ዋና አፈ ጉባኤና ምክትል አፈ ጉባኤን ጨምሮ ሌሎች በተጓደሉ ካቢኔ አባላትና ቋሚ ኮሚቴዎች ቦታ ሹመት ቀርቦ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል።
ዘጋቢ ፡ ገጶስ አየለ ከጂንካ ቅርንጫፍ!!!

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ