በዘንድሮው በ2016/17 የምርት ዘመን በበልግና በመኸር እስከአሁን ከ41ሺ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር መሸፈኑን የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።
በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ ካነጋገርናቸው አርሶ አደሮች መካከል ኑረዲን አብዱል ሽኩርና ዳዊት አሰፋ ይገኙበታል።
በሰጡት አስተያየትም በበልግና መኸር በኩታ ገጠም በማምረት ለምርጥ ዘር አቅራቢ ድርጅቶች ምርጥ ዘር እያቀረቡ ነው።
ለዚህም ውጤታማነት በባለድርሻ አካላት በኩል እየተደረገላቸው የሚገኘው ድጋፍ እና ክትትል ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳበረከተላቸው ነው አርሶ አደሮቹ የገለፁት።
የአበሽጌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ካሡ ጁሃር በዘንድሮው በ2016/17 የምርት ዘመን በበልግና በመኸር ከ60ሺ በላይ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከ41ሺ ሄክታር በላይ በተለያዩ ሰብሎች ሲለማ አብዛኛው በኩታ ገጠም አስተራረስ የተተገበረ መሆኑ በማመላከት ቀሪው ማሳ በጤፍና ሽምብራ የሚሸፈን እንደሆነም ገልፀዋል።
የምርጥ ዘርና ማዳበርያ ግብዓትን ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት መሠራቱን የገለፀት ዋና አስተዳዳሪው በቀሪ ጊዜያትም ግብዓትን በፍትሃዊነት የማዳረስ ስራ ይሰራል ብለዋል።
ዝናብ መዘግየቱን ተከትሎ በበልግ ከታረሰው 2ሺ ሄክታር ማሳ ዳግም በመዘራቱ አርሶ አደሩ፣ ባለሙያውና አመራር በጋራ መሥራት በመቻላቸው የተዘራው ሰብል አሁን ላይ በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ዘጋቢ፣ አማረ መንገሻ

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ