በገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ድጋፍ አደረጉ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖችና ቤተሰቦቻቸው የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ከ35ሺ ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ፡፡
በገዜ ጎፋ ወረዳ የደረሰውን ያልታሰበ አደጋ በማስመልከት “ለወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል የመ/ቤቱ ሰራተኞች ከወር ደሞዛቸው በመቀነስ ድጋፍ ማድረጋቸውን የደቡብ ሬዲዮና ተሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ አስረድተዋል።
የቅርንጫፍ ሬዲዮ ጣቢያው ሰራተኞች አደጋውን በማስመልከት ከደሞዛቸው በመቀነስ 35ሺ 200 ብር ለዚሁ አላማ በተከፈተው አካውንት ገቢ ማድረጋቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል።
በቀጣይም ለሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ አጋርነታቸውን በተግባር እንደሚያሳዩም ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አሰግድ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ