በገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ድጋፍ አደረጉ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖችና ቤተሰቦቻቸው የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ከ35ሺ ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ፡፡
በገዜ ጎፋ ወረዳ የደረሰውን ያልታሰበ አደጋ በማስመልከት “ለወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል የመ/ቤቱ ሰራተኞች ከወር ደሞዛቸው በመቀነስ ድጋፍ ማድረጋቸውን የደቡብ ሬዲዮና ተሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ አስረድተዋል።
የቅርንጫፍ ሬዲዮ ጣቢያው ሰራተኞች አደጋውን በማስመልከት ከደሞዛቸው በመቀነስ 35ሺ 200 ብር ለዚሁ አላማ በተከፈተው አካውንት ገቢ ማድረጋቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል።
በቀጣይም ለሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ አጋርነታቸውን በተግባር እንደሚያሳዩም ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አሰግድ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ