በገዜ ጎፋ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት ለተጎዱ ወገኖች የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ድጋፍ አደረጉ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ ለተጎዱ ወገኖችና ቤተሰቦቻቸው የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሰራተኞች ከ35ሺ ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ፡፡
በገዜ ጎፋ ወረዳ የደረሰውን ያልታሰበ አደጋ በማስመልከት “ለወገን ደራሽ ወገን ነው” በሚል የመ/ቤቱ ሰራተኞች ከወር ደሞዛቸው በመቀነስ ድጋፍ ማድረጋቸውን የደቡብ ሬዲዮና ተሌቪዥን ድርጅት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ጉጃ ጉሜ አስረድተዋል።
የቅርንጫፍ ሬዲዮ ጣቢያው ሰራተኞች አደጋውን በማስመልከት ከደሞዛቸው በመቀነስ 35ሺ 200 ብር ለዚሁ አላማ በተከፈተው አካውንት ገቢ ማድረጋቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል።
በቀጣይም ለሚደረገው ማንኛውም ድጋፍ አጋርነታቸውን በተግባር እንደሚያሳዩም ገልጸዋል።
ዘጋቢ፡ አሰግድ ተረፈ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታወቀ
የተጀመሩ የኢኒሼቲቭ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተገለጸ
የሚዛን ኤፍ.ኤም ወጣቶች የእረፍት ጊዜያቸውን ካልባሌ ቦታዎች በማራቅ በንባብና በጥናት ላይ እንዲያሳልፉ ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ገለፀ