ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑና የህብረተሰቡን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ ተግባራት በትኩረት ሊፈጸሙ እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) አመራሩ ሀገራዊ ዕድገትን የሚያፋጥኑና የህብረተሰቡን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ ተግባራትን በትኩረት መፈፀም እንዳለባቸው በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ ገለጹ፡፡
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በማህበራዊ ክላስተር ዘርፍ በ2016 ዓ.ም የተከናወኑ የመንግሥት ሥራ የአፈፃፀም ግምገማና የፓርቲ ምዘና መድረክ በጂንካ ከተማ ተካሂዷል፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አበባየሁ ታደሰ እንደገለፁት የሕብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየዘርፉ የተከናወኑት ተግባራት በመገምገም ጥንካሬና ጉድለትን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫዎች መቀመጡን ገልፀዋል ፡፡
በጤና፣ በትምህርት፣ በመስኖና ቆላማ አከባቢ ልማት፣ በሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች እንዲሁም በወጣቶችና ስፖርት ዘርፍ የታቀዱ ሥራዎች ሀገራዊ እድገትን እንዲያፋጥንና የህብረተሰቡን ችግር እንዲፈቱ አመራሩ በትኩረት መስራት እንዳለበት ዶክተር አበባየሁ አንስተው ለዘላቂነቱ ሁሉም የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፡፡
በአፈፃፀም ግምገማ የተነሡ ሀሳቦችን በመተግበር የተሻለ አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንዲሚሠሩ የመድረኩ ተሳታፊ አመራሮች ገልፀዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ