ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርላማ አባላትና የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት አባላት በጋራ የሚያከናውኑትን የህዝብ ውክልና ስራ በማስመልከት ውይይት በማድረግ ላይ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡
የህዝብ ተወካዮቹ በቀጣይ ቀናት ወደ ምርጫ ክልሎቻቸው በመንቀሳቀስ ከነዋሪዎች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ የሚጠበቅ ሲሆን ውይይቱ የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች አሁናዊ ሁኔታ ይፈተሻል።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ሰርሞሎ ባለፈው የካቲት ወር 22ሺ 800 የህብረተሰብ ክፍሎች ከተወካዮቻቸው ጋር መወያየታቸውን ጠቁመዋል።
በነበረው ህዝባዊ ውይይት በርካታ የመልማት ጥያቄዎች ተነስተው የነበረ ሲሆን የምክር ቤቱ አባላት የአፈፃፀማቸውን ደረጃ ሲከታተል መቆየቱን አብራርተዋል።
የዛሬው መድረክም ለቀጣይ የህዝብ ውክልና ስራ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ የሚመክርና አጠቃላይ የህዝቦች ጥያቄ እና የተሰጡ ምላሾችን የሚፈትሽ ስለመሆኑ አመላክተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ
More Stories
ለወንጀል ድርጊት አመቺ የሆኑ ቦታዎችን በመቃኘት በአካባቢው ያለውን ሠላም በዘላቂነት ለማስቀጠል እየተሠራ ነው – የዲላ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት
የዘይሴ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ ” ቡዶ ከሶ” በዓል በድምቀት ተከበረ
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የተከተሉት የሰከነ የፖለቲካ ትግል ስልት በአርዓያነት የሚወሰድ መሆኑ ተገለጸ