ሀዋሳ፡ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፓርላማ አባላትና የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት አባላት በጋራ የሚያከናውኑትን የህዝብ ውክልና ስራ በማስመልከት ውይይት በማድረግ ላይ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡
የህዝብ ተወካዮቹ በቀጣይ ቀናት ወደ ምርጫ ክልሎቻቸው በመንቀሳቀስ ከነዋሪዎች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ የሚጠበቅ ሲሆን ውይይቱ የህዝቡን የመልማት ጥያቄዎች አሁናዊ ሁኔታ ይፈተሻል።
በዚህ ወቅት ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ሰርሞሎ ባለፈው የካቲት ወር 22ሺ 800 የህብረተሰብ ክፍሎች ከተወካዮቻቸው ጋር መወያየታቸውን ጠቁመዋል።
በነበረው ህዝባዊ ውይይት በርካታ የመልማት ጥያቄዎች ተነስተው የነበረ ሲሆን የምክር ቤቱ አባላት የአፈፃፀማቸውን ደረጃ ሲከታተል መቆየቱን አብራርተዋል።
የዛሬው መድረክም ለቀጣይ የህዝብ ውክልና ስራ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ የሚመክርና አጠቃላይ የህዝቦች ጥያቄ እና የተሰጡ ምላሾችን የሚፈትሽ ስለመሆኑ አመላክተዋል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ