ሀዋሳ፡ ነሐሴ 09/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አድማሱ ማሴቦ በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት ምክር ቤቶች የህዝብን ሉዓላዊነት ከማስከበር ባሻገር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራሉ ።
መንግስት ያጎናፀፈውን በልዩ ወረዳ የመደራጀት መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በቅርቡ በልዩ ወረዳው የጠምባሮ ልማት ማህበር መቋቋም ከተከናወኑ ተግባራት አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ዋና አፈ-ጉባኤው በቀጣይም የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮችን በማደራጀት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር ከተረጅነት ለመላቀቅ የሚያስችሉ ስራዎች ከአመራሩና ከህብረተሰቡ የሚጠበቁ ስለመሆናቸውም ዋና አፈ-ጉባኤው አመላክተዋል።
ጉባኤው የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የበጀት ዓመቱን የስራ አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የስራ ዘመን ዕቅድ ላይ ውይይት ያደርጋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚካሄደው ጉባኤው የ2016 አፈፃፀም ሪፖርት በመገምገም የ2017 የስራ ዘመን ጠቋሚ ዕቅድና ማስፈፀሚያ በጀት ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ ፡ አማኑኤል አጤቦ ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶችን የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ለመቅረፍ የተጀመሩ ጥረቶችን ለማጎልበት የጤና አደረጃጀቶችን ሚና ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመግባት ዕድል ያገኙ ተማሪዎች የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ትምህርታቸው ላይ ብቻ ሊያተኩሩ እንደሚገባ መልዕክት ተላለፈ
የሀዲያ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለ2018 በጀት ዓመት ከ10 ቢልዮን ብር በላይ በጀት ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውል በተገቢው እንደሚሠራ ገለፀ