ሀዋሳ፡ ነሐሴ 09/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አድማሱ ማሴቦ በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት ምክር ቤቶች የህዝብን ሉዓላዊነት ከማስከበር ባሻገር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራሉ ።
መንግስት ያጎናፀፈውን በልዩ ወረዳ የመደራጀት መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በቅርቡ በልዩ ወረዳው የጠምባሮ ልማት ማህበር መቋቋም ከተከናወኑ ተግባራት አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ዋና አፈ-ጉባኤው በቀጣይም የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮችን በማደራጀት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር ከተረጅነት ለመላቀቅ የሚያስችሉ ስራዎች ከአመራሩና ከህብረተሰቡ የሚጠበቁ ስለመሆናቸውም ዋና አፈ-ጉባኤው አመላክተዋል።
ጉባኤው የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የበጀት ዓመቱን የስራ አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የስራ ዘመን ዕቅድ ላይ ውይይት ያደርጋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚካሄደው ጉባኤው የ2016 አፈፃፀም ሪፖርት በመገምገም የ2017 የስራ ዘመን ጠቋሚ ዕቅድና ማስፈፀሚያ በጀት ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ ፡ አማኑኤል አጤቦ ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ