ሀዋሳ፡ ነሐሴ 09/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጠምባሮ ልዩ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ አድማሱ ማሴቦ በመግቢያ ንግግራቸው ወቅት እንደገለፁት ምክር ቤቶች የህዝብን ሉዓላዊነት ከማስከበር ባሻገር የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት ይሰራሉ ።
መንግስት ያጎናፀፈውን በልዩ ወረዳ የመደራጀት መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በቅርቡ በልዩ ወረዳው የጠምባሮ ልማት ማህበር መቋቋም ከተከናወኑ ተግባራት አንዱ መሆኑን የጠቆሙት ዋና አፈ-ጉባኤው በቀጣይም የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮችን በማደራጀት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር ከተረጅነት ለመላቀቅ የሚያስችሉ ስራዎች ከአመራሩና ከህብረተሰቡ የሚጠበቁ ስለመሆናቸውም ዋና አፈ-ጉባኤው አመላክተዋል።
ጉባኤው የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የበጀት ዓመቱን የስራ አፈፃፀም በመገምገም በቀጣይ የስራ ዘመን ዕቅድ ላይ ውይይት ያደርጋል።
ከዛሬ ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚካሄደው ጉባኤው የ2016 አፈፃፀም ሪፖርት በመገምገም የ2017 የስራ ዘመን ጠቋሚ ዕቅድና ማስፈፀሚያ በጀት ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ዘጋቢ ፡ አማኑኤል አጤቦ ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ