በክረምት የሚተገበሩ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት የበርካታ ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እየፈታ መሆኑ ተገለፀ

በክረምት የሚተገበሩ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት የበርካታ ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እየፈታ መሆኑ ተገለፀ

ሀዋሳ፡ ነሐሴ 08/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በክረምት የሚተገበሩ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት የበበርካታ ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እየፈታ መሆኑ ተገልጿል።

የጂንካ አጠቃላይ አጠቃላይ ሆስፒታል “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ነፃ የክረምት በጎ ፈቃድ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር አካሂዷል።

ሲ/ር  ባንችወሰን አሰፋ ሆስፒታሉ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የደም ልገሳን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰዋል።

ቤታቸው የሚታደስላቸው ወ/ሮ አልማዝ ጎመጆ ደሳሳ ሳር ቤታቸው ዝናብና ፀሐይ ስፈራረቅ በጣም ተጨንቀው ይጠለሉ እንደነበረ ገልፀው በጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታሉ ለሚያደርግላቸው በጎ ሥራ አመስግነዋል።

የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ብርክታዊት አሰፋ ሆስፒታሉ ከመደበኛ የህክምና አገልግሎት ባሻገር በበጎ ተግባር በስፋት እየተሳተፈ ይገኛል ይህንንም አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልፀዋል።

በሥራው የተሳተፉና ያስተባበሩ አካላትም በተግባራቸው ደስተኞች መሆናቸውን ገልፀው ድጋፍ ለሚሹ አካላት ቀጣይነት ያለው በጎ ሥራ እንደሚደረግላቸውም ገልፀዋል።

ዘጋቢ:  ተመስገን አበራ – ከጂንካ ጣቢያችን