ሀዋሳ፡ 07/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የዳዉሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባዔ እያካሄደ ይገኛል።
በዞኑ ምክር ቤት ጉባዔ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ዋና አፈ ጉባዔ አቶ ዳዊት ሚኖታ በየደረጃው የሚገኙ ምክር ቤቶች የሕዝብ ሉዑላዊነት መገለጫና ቀጥተኛ የሕዝብ ውክልና ይዘው የሚሠሩ ናቸው።
በመሆኑም ምክር ቤቶች በተሰጣቸው ኃላፊነት ተግባራቸውን ሕግና ሥርዓት ባለው ሁኔታ እንዲሠሩ የተቀናጀ ጥረትን ይጠይቃልም ብለዋል።
የዞኑ ምክር ቤት በሕገ መንግሥቱ በተሰጠው ሥልጣን የአስፈጻሚዎችን ዕቅድ አፈጻጸም በመገምገም ለሕዝቡ ለውጥና ዕድገት እንዲሁም ለውጤታማነት እየሠራ እንዳለ በመጠቆም።
በመሆኑም ዞኑን ባጋጠመው የበጀት እጥረትና በሌሎችም ምክንያቶች አልፎ አልፎ በአንዳንድ ወረዳዎችና ቀበሌያት ከአስቸኳይ ጉባዔ ውጪ መደበኛ ጉባዔዎች እየተካሄዱ አለመሆናቸውን አብራርተዋል።
ስለሆነም በቀጣይ የሚታዩ ችግሮችን በመቅረፍ ለውጤታማነትና ለሕዝብ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት በተቀናጀ ጥረት ሊሠራ እንደሚገባም አብራርተዋል።
ጉባዔው ያለፈውን ዓመት ጉባዔ ቃለ ጉባዔ፣ የ2017 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድና የሥራ ዘመኑን የበጀት ረቂቅ አዋጅና መግለጫ፣ የዳዉሮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዕቅድ አፈጻጸም፣ የአሠራርና የአባላት ሥነ ምግባር ደንብ፣ የቋሚ ኮሚቴ አባላት ማሟያ ምርጫና የዞኑ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት ሹመት መርምሮ እንደሚያጸድቅ የምክር ቤቱ መርሀግብር ያመለክታል
ዘጋቢ፡ መሣይ መሠለ- ከዋካ ቅርንጫፍ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ