ሦስት ኢትዮጵያዊ አትሌቶች በዛሬው የግማሽ ፍፃሜ ውድድራቸውን ያካሂዳሉ
በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የግማሽ ፍፃሜ ሩጫ ሦስት ኢትዮጵያዊ አትሌቶች ዛሬ ምሽት ይወዳደራሉ።
ምሽት 2 ሰዓት ከ35 ላይ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ አትሌት ደርቤ ወልተጂና አትሌት ብርቄ ሃየሎም በኢትዮጵያ በኩል ተወዳዳሪዎች ናቸው።
ቅዳሜ ምሽት 3 ሰዓት ከ35 ላይ ለሚካሄደው የፍፃሜ ውድድር ለማለፍ አትሌት ብርቄ ሐየሎም በመጀመሪያው ምድብ እንዲሁም አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬና ድርቤ ወልተጂ በሁለተኛው ምድብ ተደልድለው የግማሽ ፍፃሜ ውድድራቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል ክርስቶስ ዞሊስን ለማስፈረም ተስማማ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በወልቂጤ ከተማ የሰርከስ ስፖርት ምልመላና የማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት መርሃ ግብር ተካሄደ
አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል እንግሊዝ ወደ ፍፃሜ ባለማለፏ ከፍተኛ ትችትን አስተናገዱ