ሦስት ኢትዮጵያዊ አትሌቶች በዛሬው የግማሽ ፍፃሜ ውድድራቸውን ያካሂዳሉ
በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የግማሽ ፍፃሜ ሩጫ ሦስት ኢትዮጵያዊ አትሌቶች ዛሬ ምሽት ይወዳደራሉ።
ምሽት 2 ሰዓት ከ35 ላይ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ አትሌት ደርቤ ወልተጂና አትሌት ብርቄ ሃየሎም በኢትዮጵያ በኩል ተወዳዳሪዎች ናቸው።
ቅዳሜ ምሽት 3 ሰዓት ከ35 ላይ ለሚካሄደው የፍፃሜ ውድድር ለማለፍ አትሌት ብርቄ ሐየሎም በመጀመሪያው ምድብ እንዲሁም አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬና ድርቤ ወልተጂ በሁለተኛው ምድብ ተደልድለው የግማሽ ፍፃሜ ውድድራቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
የሀገሪቱን ቦክስ ስፖርት ለማሳደግ የቀድሞ ቦክሰኞችና ሌሎችም አስተዋጽዋቸውን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ ጥሪ ቀረበ
2ኛው የየም ዞን ስፖርት ሻምፕዮና በሣጃ ከተማ እየተካሄደ ነው
የ2017 የጋሞ ዞን ልዩ ልዩ ስፖርቶች ሻምፒዮና ውድድር በወንዶች እግር ኳስ ውድድር በዳራማሎ ወረዳ አሸናፊነት ተጠናቀቀ