ሦስት ኢትዮጵያዊ አትሌቶች በዛሬው የግማሽ ፍፃሜ ውድድራቸውን ያካሂዳሉ
በ33ኛው የፓሪስ ኦሎምፒክ የ1 ሺህ 500 ሜትር ሴቶች የግማሽ ፍፃሜ ሩጫ ሦስት ኢትዮጵያዊ አትሌቶች ዛሬ ምሽት ይወዳደራሉ።
ምሽት 2 ሰዓት ከ35 ላይ በሚካሄደው የግማሽ ፍፃሜ ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ አትሌት ደርቤ ወልተጂና አትሌት ብርቄ ሃየሎም በኢትዮጵያ በኩል ተወዳዳሪዎች ናቸው።
ቅዳሜ ምሽት 3 ሰዓት ከ35 ላይ ለሚካሄደው የፍፃሜ ውድድር ለማለፍ አትሌት ብርቄ ሐየሎም በመጀመሪያው ምድብ እንዲሁም አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬና ድርቤ ወልተጂ በሁለተኛው ምድብ ተደልድለው የግማሽ ፍፃሜ ውድድራቸውን የሚያካሂዱ ይሆናል።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
አርሰናል በአስቶንቫላ ተሸነፈ
ኮቢ ሜይኑ ማንቸስተር ዩናይትድን መልቀቅ ይፈልጋል
በመላ አፍሪካ ርዕሰ ከተሞች መካከል፣ ለዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲና የጋራ አህጉራዊ ተቋማት ማዕከል በሆነችው ምድራችን፣ ታላቅ የሚዲያ መድረክ ማስተናገድ ታላቅ ኩራት ነው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት