በደቡብ  ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ  ዞን ሽግግር ምክር ቤት ለ2017 በጀት አመት ከ1 ቢሊዬን 497 ሚሊዬን ብር በላይ በጀት በማፅደቅና ውሳኔዎችን በማሳለፍ  ጉባኤውን አጠናቀቀ

በደቡብ  ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ  ዞን ሽግግር ምክር ቤት ለ2017 በጀት አመት ከ1 ቢሊዬን 497 ሚሊዬን ብር በላይ በጀት በማፅደቅና ውሳኔዎችን በማሳለፍ  ጉባኤውን አጠናቀቀ

የህዝብና የመንግሥት  ውስን ሀብትን በአግባቡ  በመምራት  የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት  ለማረጋገጥ  በየደረጃው  የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በትኩረት መሥራት እንዳለባቸው የምክር ቤቱ ዋና አፌ ጉባኤ ወይዘሮ  ስመኝ ተስፋዬ  አሳስበዋል ፡፡

የምክር ቤቱ አባላት በጥንካሬና በድክመት  የታዩ አፈፃፀሞች ላይ አስተያየትና ጥያቄዎችን አንስተው በግብርና  ፣በኢንቨስትመንት እንዲሁም በመሠረተ ልማት ዘርፍ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በቅርበት  ክትትል እንደሚያደርጉ ገልፀዋል ፡፡

ከሕብረተሰቡ  የሚሰበሰቡና ከመንግሥት  የሚመደበው  ውስን በጀት በቁጠባ ለታለመለት ዓላማ በማዋል የልማት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ሊሠራ ይገባል  ብለዋል፡፡

የዞኑ የ2017 በጀት ዓመት ሥራ ማስፈፀሚያ 1 ቢሊዬን 497 ሚሊዬን 337 ሺህ 317 ብር ጸድቋል ፡፡

 የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ  አቶ አብርሃም  አታ ገልፀው  የውስጥ ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ  በጀቱ ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ክትትል ይደረጋል ብለዋል፡፡

የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፌጉባኤ ወይዘሮ ስመኝ ተስፋዬ  እንደገለፁት ውስን ሀብትን  በአግባቡ  በመምራት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት  ለማረጋገጥ  በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በትኩረት እንዲሠሩ አሳስበዋል ፡፡

ምክር ቤቱ  የቀረቡለትን ሹመቶችን በማፅደቅ  ተጠናቋል ፡፡

ዘጋቢ – ተመስገን አሰፋ-ከጂንካ ጣቢያችን