የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ እንደገለፁት ምክር ቤቱ በህገመንግሥቱ በተሰጠው ኃላፊነት የህግ አስፈፃሚውና የህግ ተርጓሚው ሥራ በመቆጣጠርና በመከታተል ለዜጎች ተጠቃሚነት በርካታ ተግባራት አከናውኗል፡፡
የዜጎችን ሠላምና ደህነት ለማስጠበቅ እየተሠሩ ያሉ መልካም ጅምሮችን ለማጠናከር ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
በማህበራዊና በኢኮኖሚ እንዲሁም በህግ ፍትህና መልካም አስተዳደር ዘርፎች ለዜጎች ፍትሐዊና ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት የምክር ቤቱ አባላት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አፈጉባኤዋ አሳስበዋል፡፡
ምክር ቤቱ በሁለት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ