የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ እንደገለፁት ምክር ቤቱ በህገመንግሥቱ በተሰጠው ኃላፊነት የህግ አስፈፃሚውና የህግ ተርጓሚው ሥራ በመቆጣጠርና በመከታተል ለዜጎች ተጠቃሚነት በርካታ ተግባራት አከናውኗል፡፡
የዜጎችን ሠላምና ደህነት ለማስጠበቅ እየተሠሩ ያሉ መልካም ጅምሮችን ለማጠናከር ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
በማህበራዊና በኢኮኖሚ እንዲሁም በህግ ፍትህና መልካም አስተዳደር ዘርፎች ለዜጎች ፍትሐዊና ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት የምክር ቤቱ አባላት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አፈጉባኤዋ አሳስበዋል፡፡
ምክር ቤቱ በሁለት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
በ17 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሞሪንጋ ጂን ባንክ ለማቋቋም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ