የኣሪ ዞን ሽግግር ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ እንደገለፁት ምክር ቤቱ በህገመንግሥቱ በተሰጠው ኃላፊነት የህግ አስፈፃሚውና የህግ ተርጓሚው ሥራ በመቆጣጠርና በመከታተል ለዜጎች ተጠቃሚነት በርካታ ተግባራት አከናውኗል፡፡
የዜጎችን ሠላምና ደህነት ለማስጠበቅ እየተሠሩ ያሉ መልካም ጅምሮችን ለማጠናከር ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
በማህበራዊና በኢኮኖሚ እንዲሁም በህግ ፍትህና መልካም አስተዳደር ዘርፎች ለዜጎች ፍትሐዊና ተደራሽ አገልግሎት በመስጠት የምክር ቤቱ አባላት የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አፈጉባኤዋ አሳስበዋል፡፡
ምክር ቤቱ በሁለት ተከታታይ ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ዘጋቢ፡ ተመስገን አሰፋ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ