የብልፅግና ፓርቲ ስራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ገቡ
ሚንስትሯ ወደ ሆሳዕና ሲደርሱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በሆሳዕና ቆይታቸው 2017 በጀት ዓመት የሥራ ዕድል ፈጠራ መስኮች ላይ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ካቢኔ አባላት ጋር ዉይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከሚኒስትሯ ጋር የሚኒስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች፣ ሚኒስትር ዲኤታዎች እና የማኔጅመንት አባላትም ተገኝተዋል።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ