የብልፅግና ፓርቲ ስራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ገቡ
ሚንስትሯ ወደ ሆሳዕና ሲደርሱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በሆሳዕና ቆይታቸው 2017 በጀት ዓመት የሥራ ዕድል ፈጠራ መስኮች ላይ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ካቢኔ አባላት ጋር ዉይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከሚኒስትሯ ጋር የሚኒስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች፣ ሚኒስትር ዲኤታዎች እና የማኔጅመንት አባላትም ተገኝተዋል።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ

More Stories
በጎፋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ጥራትና ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታወቀ
የተጀመሩ የኢኒሼቲቭ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተገለጸ