የብልፅግና ፓርቲ ስራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ገቡ
ሚንስትሯ ወደ ሆሳዕና ሲደርሱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በሆሳዕና ቆይታቸው 2017 በጀት ዓመት የሥራ ዕድል ፈጠራ መስኮች ላይ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ካቢኔ አባላት ጋር ዉይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከሚኒስትሯ ጋር የሚኒስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች፣ ሚኒስትር ዲኤታዎች እና የማኔጅመንት አባላትም ተገኝተዋል።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ
More Stories
ፈጣንና ቀልጣፋ መረጃን ተጀራሽ በማድረግ የመንግስትና የማህበረሰቡን ተግባቦት ይበልጥ ለማጠናከር የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
ሀገር አቀፍ የጥናትና ምርምር ኮንፍረንስ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው
በ17 ነጥብ 5 ሄክታር መሬት ላይ የሞሪንጋ ጂን ባንክ ለማቋቋም ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ