የብልፅግና ፓርቲ ስራ አሰፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ ገቡ
ሚንስትሯ ወደ ሆሳዕና ሲደርሱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በሆሳዕና ቆይታቸው 2017 በጀት ዓመት የሥራ ዕድል ፈጠራ መስኮች ላይ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ካቢኔ አባላት ጋር ዉይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከሚኒስትሯ ጋር የሚኒስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች፣ ሚኒስትር ዲኤታዎች እና የማኔጅመንት አባላትም ተገኝተዋል።
ዘጋቢ: ጀማል የሱፍ
More Stories
አካል ጉዳተኞች መብቶቻቸውና ጥቅሞቻቸውን ለማስጠበቅ በቅንጅትና በጥምረት መስራት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ገለፀ
አካባቢን በመጠበቅና በማጽዳት ምቹና ጽዱ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት በማገዝ ሁሉም የድርሻውን ልወጣ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር እንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ
ግለሰባዊ ነጠላ ትርክቶችን በጋራ በመታገል በመደመር እሳቤ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ ተገለጸ