በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባደረጉት ንግግር በክልሉና በዞኑ አስተዳደር ወደስራ የገባው የሬዲዮ ጣቢያው የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የመለሰ ነው ብለዋል።
የማሻ ኤፍ ኤም 103.8 ከማዝናናትና መረጃ ከመስጠት በተጨማሪ አካባቢው ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ የሚማርኩ መልክዓ ምድርና የመስህቦች ባለቤት በመሆኑ ለአለም ማስተዋወቅ እንደሚገባውም አንስተዋል።
ክልሉ ሚዲያ ኔትወርክ በማደራጀት ወደስራ የማስገባት ሂደት ላይ እንደሚገኝም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል፡፡
የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ በበኩላቸው የህዝብን የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲረጋገጡ አዳዲስ ሀሳቦችን በማፍለቅ የሬዲዮ ጣቢያው ለህብረተሰቡ ተስፋ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
በምረቃው ፕሮግራሙ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ እና ሌሎች የፌደራል፣ የክልል፣ የሸካ ባህላዊ አስተዳደር፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለድርሻ ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ልጃለም ማሞ – ከማሻ ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ