በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ባደረጉት ንግግር በክልሉና በዞኑ አስተዳደር ወደስራ የገባው የሬዲዮ ጣቢያው የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የመለሰ ነው ብለዋል።
የማሻ ኤፍ ኤም 103.8 ከማዝናናትና መረጃ ከመስጠት በተጨማሪ አካባቢው ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ የሚማርኩ መልክዓ ምድርና የመስህቦች ባለቤት በመሆኑ ለአለም ማስተዋወቅ እንደሚገባውም አንስተዋል።
ክልሉ ሚዲያ ኔትወርክ በማደራጀት ወደስራ የማስገባት ሂደት ላይ እንደሚገኝም ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል፡፡
የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ በበኩላቸው የህዝብን የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እንዲረጋገጡ አዳዲስ ሀሳቦችን በማፍለቅ የሬዲዮ ጣቢያው ለህብረተሰቡ ተስፋ ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
በምረቃው ፕሮግራሙ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ ወንድሙ ኩርታ እና ሌሎች የፌደራል፣ የክልል፣ የሸካ ባህላዊ አስተዳደር፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮችና ባለድርሻ ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ልጃለም ማሞ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
በጎፋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ጥራትና ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታወቀ
የተጀመሩ የኢኒሼቲቭ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተገለጸ