የሆሳዕና ወርልድ ብራይት ኮሌጅ ለ6ኛ ዙር በድፕሎማ፣በመጀመሪያ ድግሪና በሁለተኛ ድግሪ በተለያዩ የስልጠና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2ሺ783 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው

የሆሳዕና ወርልድ ብራይት ኮሌጅ ለ6ኛ ዙር በድፕሎማ፣በመጀመሪያ ድግሪና በሁለተኛ ድግሪ በተለያዩ የስልጠና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2ሺ783 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው

ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከተማራቂዎቹ 1ሺ87 ወንዶች ሲሆኑ 1ሺ699ኙ ሴቶች መሆናቸውን ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የምረቃ መርኃግብሩን በእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት የከፈቱት የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ዶክተር ተሰማ አበራ ኮሌጁ በሀገሪቱ በዕውቀትና ክህሎት የበቃ የሰው ኃይል በመፍጠር በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ መሆንን ዓላማ አድርጎ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በምረቃ መርኃግብሩ ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት እንስትትዩት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃሌፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡

ዘጋቢ፡ ሳሙኤል መንታሞ- ከሆሳዕና ጣቢያችን