የሆሳዕና ወርልድ ብራይት ኮሌጅ ለ6ኛ ዙር በድፕሎማ፣በመጀመሪያ ድግሪና በሁለተኛ ድግሪ በተለያዩ የስልጠና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2ሺ783 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከተማራቂዎቹ 1ሺ87 ወንዶች ሲሆኑ 1ሺ699ኙ ሴቶች መሆናቸውን ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
የምረቃ መርኃግብሩን በእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት የከፈቱት የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ዶክተር ተሰማ አበራ ኮሌጁ በሀገሪቱ በዕውቀትና ክህሎት የበቃ የሰው ኃይል በመፍጠር በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ መሆንን ዓላማ አድርጎ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በምረቃ መርኃግብሩ ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት እንስትትዩት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃሌፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል መንታሞ- ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ