የሆሳዕና ወርልድ ብራይት ኮሌጅ ለ6ኛ ዙር በድፕሎማ፣በመጀመሪያ ድግሪና በሁለተኛ ድግሪ በተለያዩ የስልጠና መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2ሺ783 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ከተማራቂዎቹ 1ሺ87 ወንዶች ሲሆኑ 1ሺ699ኙ ሴቶች መሆናቸውን ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
የምረቃ መርኃግብሩን በእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት የከፈቱት የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ዶክተር ተሰማ አበራ ኮሌጁ በሀገሪቱ በዕውቀትና ክህሎት የበቃ የሰው ኃይል በመፍጠር በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ መሆንን ዓላማ አድርጎ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በምረቃ መርኃግብሩ ፕሮፌሰር በየነ ጼጥሮስ የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት እንስትትዩት ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃሌፊዎች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
ዘጋቢ፡ ሳሙኤል መንታሞ- ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የብልጽግና ፓርቲ አዳዲስ ኢኒሼቲቮችን በመፍጠር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ሥራዎችን እየተገበረ ይገኛል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የጂንካ ከተማ አስተዳደር የኦንላይን ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በይፋ ስራ ጀመረ
ዜጎች ሠላማቸው ተጠብቆ በነጻነት ምርጫን ማካሄድ እንዲችሉ ፖሊስ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ