ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናንተዋል፡፡
ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
ሰው ለማዳን በሄዱበተ ውድ ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች ሃዘን ልብ ሰባሪ ነው ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው እስካሁን የቤተሰብ አባል ይመጣል እያሉ የሚጠብቁ ሰዎች መኖራቸውን አንስተው አደጋው ልብ ሰባሪ እንደሆነ ገልፀው ኢትዮጵያውያን ላደረጉት ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል።
በቀጣይም ተጎጂዎችን በዘላቂነት ማቋቋም ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል።
የመቶዎችን ህይወት የቀጠፈው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓም ማለዳ በጎፋ ዞን ሻቻ ኪንቾ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዴሊ በተባለ ስፍራ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በጎፋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ጥራትና ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታወቀ
የተጀመሩ የኢኒሼቲቭ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተገለጸ