ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናንተዋል፡፡
ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
ሰው ለማዳን በሄዱበተ ውድ ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች ሃዘን ልብ ሰባሪ ነው ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው እስካሁን የቤተሰብ አባል ይመጣል እያሉ የሚጠብቁ ሰዎች መኖራቸውን አንስተው አደጋው ልብ ሰባሪ እንደሆነ ገልፀው ኢትዮጵያውያን ላደረጉት ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል።
በቀጣይም ተጎጂዎችን በዘላቂነት ማቋቋም ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል።
የመቶዎችን ህይወት የቀጠፈው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓም ማለዳ በጎፋ ዞን ሻቻ ኪንቾ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዴሊ በተባለ ስፍራ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ