ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናንተዋል፡፡
ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
ሰው ለማዳን በሄዱበተ ውድ ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች ሃዘን ልብ ሰባሪ ነው ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው እስካሁን የቤተሰብ አባል ይመጣል እያሉ የሚጠብቁ ሰዎች መኖራቸውን አንስተው አደጋው ልብ ሰባሪ እንደሆነ ገልፀው ኢትዮጵያውያን ላደረጉት ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል።
በቀጣይም ተጎጂዎችን በዘላቂነት ማቋቋም ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል።
የመቶዎችን ህይወት የቀጠፈው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓም ማለዳ በጎፋ ዞን ሻቻ ኪንቾ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዴሊ በተባለ ስፍራ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ