ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናኑ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች በስፍራው ተገኝተው አፅናንተዋል፡፡
ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።
ሰው ለማዳን በሄዱበተ ውድ ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች ሃዘን ልብ ሰባሪ ነው ያሉት የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው እስካሁን የቤተሰብ አባል ይመጣል እያሉ የሚጠብቁ ሰዎች መኖራቸውን አንስተው አደጋው ልብ ሰባሪ እንደሆነ ገልፀው ኢትዮጵያውያን ላደረጉት ርብርብ ምስጋና አቅርበዋል።
በቀጣይም ተጎጂዎችን በዘላቂነት ማቋቋም ላይ ትኩረት ይደረጋል ብለዋል።
የመቶዎችን ህይወት የቀጠፈው የመሬት መንሸራተት አደጋ ሀምሌ 15 ቀን 2016 ዓም ማለዳ በጎፋ ዞን ሻቻ ኪንቾ ቀበሌ ልዩ ስሙ ዴሊ በተባለ ስፍራ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
ዘጋቢ: ሲሳይ ደበበ

More Stories
የብልጽግና ፓርቲ አዳዲስ ኢኒሼቲቮችን በመፍጠር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ሥራዎችን እየተገበረ ይገኛል – አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የጂንካ ከተማ አስተዳደር የኦንላይን ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በይፋ ስራ ጀመረ
ዜጎች ሠላማቸው ተጠብቆ በነጻነት ምርጫን ማካሄድ እንዲችሉ ፖሊስ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ