546 ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴን ማክሸፍ ተችሏል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ፡ ሀምሌ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉን ሠላም ለማወክ የሚንቀሳቀሱ 546 ሀሰተኛ ማህበራዊ ሚዲያዎችን አላማ ማክሸፍ መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እያካሄደ ባለው 6ዙር 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ጉባኤው ላይ ተገኝተው የክልሉን የ2016 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል።
በሪፖርታቸውም የክልሉን ሠላም ለማወክ አላማ አድርገው የተነሱ 546 ማህበራዊ ሚዲያዎችን መግታት ተችሏል ብለዋል።
ሚዲያዎቹ ክልሉ እንዳይረጋጋ ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውን በተደረገ ክትትል መረጋጉጡን አስታውቀዋል።
አክለውም በክልሉ የወንጀል መጠን 10 በመቶ ለመቀነስ ታቅዶ 11 በመቶ መሠራቱን አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ