ባለፈው በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው

ባለፈው በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው

ሀዋሳ፡ ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2016 በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የበጀት አመቱን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛል።

በሪፖርታቸውም በ2016 በጀት አመት በክልሉ 12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሠብሠቡን ገልጸዋል።

አፈፃፀሙ 87 ነጥብ 4 በመቶ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከአምናው ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል።

ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ