ባለፈው በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2016 በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የበጀት አመቱን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛል።
በሪፖርታቸውም በ2016 በጀት አመት በክልሉ 12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሠብሠቡን ገልጸዋል።
አፈፃፀሙ 87 ነጥብ 4 በመቶ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከአምናው ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
የሃገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
አርሶ አደሩ በእንሰት ተክል የምግብ ዋስትናውን በማረጋገጥ የኢኮኖሚ አቅሙን እንድያሳድግ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
ህብረት ሥራ ማህበራት ለሀገር ብልፅግና መሪ ተዋናይ ናቸው ሲል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህብረት ሥራ ልማት ኤጀንሲ ገለፀ