ባለፈው በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2016 በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የበጀት አመቱን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛል።
በሪፖርታቸውም በ2016 በጀት አመት በክልሉ 12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሠብሠቡን ገልጸዋል።
አፈፃፀሙ 87 ነጥብ 4 በመቶ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከአምናው ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
በክልሉ ከተለያዩ መገናኛ ብዙኃን የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን በሚዛን አማን ከተማ አረንጓዴ አሻራ አሳረፉ
የሲዳማ ክልላዊ መንግሥት 5ኛ አመት የምስረታ በዓል በተለያዩ ስነ ስርዓቶች እየተከበረ ነው
በክልሉ በተያዘው የበልግ ወቅት በኩታገጠም ሩዝና በቆሎ እያለሙ ያሉ አርሶአደሮች ተስፋ ሰጪ የሆነ የምርት ውጤት እንድናይ አስችሎናል አሉ።