ባለፈው በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2016 በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የበጀት አመቱን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛል።
በሪፖርታቸውም በ2016 በጀት አመት በክልሉ 12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሠብሠቡን ገልጸዋል።
አፈፃፀሙ 87 ነጥብ 4 በመቶ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከአምናው ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በጎፋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ጥራትና ተዓማኒነት ያለው የፍትህ አገልግሎት በመስጠት ረገድ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የዞኑ ፍትህ መምሪያ አስታወቀ
ለህብረተሰቡ ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታወቀ
የተጀመሩ የኢኒሼቲቭ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያመጡ መሆኑ ተገለጸ