ባለፈው በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ተሰብስቧል – ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2016 በጀት አመት 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ የበጀት አመቱን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለክልሉ ምክር ቤት እያቀረቡ ይገኛል።
በሪፖርታቸውም በ2016 በጀት አመት በክልሉ 12 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሠብሠቡን ገልጸዋል።
አፈፃፀሙ 87 ነጥብ 4 በመቶ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ከአምናው ተመሣሣይ ወቅት ጋር ሲነፃጸር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ አሳይቷል ብለዋል።
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ለ6ኛ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ላይ ለመካፈል ተመረጠ!
ከባዶነት ወደ እሳታማ ድባብ፦ ሚኬል አርቴታ የኤምሬትስን መንፈስ እንዴት ቀየረው?
የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም ከተሞችን ፅዱና ምቹ ከማድረግ ባሻገር የኤክስፖርት ምርትን ማሳደግ እንደሚያስፈልግ የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ገለጸ