የጂንካ ዩኒቨርስቲ ለ4ተኛ ጊዜ በመጀመሪያ ዲግሪና ለመጀመሪያ ጊዜ ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 871 ተማሪዎች አስመረቀ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የጂንካ ዩኒቨርስቲ ለ4ተኛ ጊዜ በመጀመሪያ ዲግሪና ለመጀመሪያ ጊዜ ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 871 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡
ከተመራቂ ተማሪዎቹ ውስጥ ወንድ 637 ሴት 139 በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ ሴት 16 ወንድ 69 በድምሩ 85 ተማሪዎቾ መመረቃቸው ታውቋል።
የእለቱ የክብር እንግዳና የጂንካ ዩኒቨርስቲ የስራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰበሳቢ የሆኑት ኘሮፌሰር አሰፋ አስማረ ባስተላለፉት መልእክት የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋችሁ ለዚህ ክብር በመብቃታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ካሉ በኋላ ተመራቂ ተማሪዎች ከትምህርት ዓለም ወደ ስራ ዓለም የምትሠማሩበት ወቅት በመሆኑ የሚያጋጥሟችሁን ፈተናዎች በብርታትና በትጋት በመጋፈጥ የሕይወት ዘመን ፈተናዎቻችሁን በብቃት መሻገር ይጠበቅባችኋል ብለዋል።
ኘሮፌሰር አሰፋ አስማረ ጨምረው እንዳሉት ተመራቂ ተማሪዎች በሃገር እድገትና ልማት ላይ ደርሻችሁ ከፍተኛ በመሆኑ በተመረቃችሁበት የትምህርት መስክ ሕዝብና ሃገር የማገልገል አደራ ተጥሎባችኋል ሲሉም ተናግረዋል።
የጂንካ ዩኒቨርስቲ ኘሬዝዳንት ዶ/ር ኩሴ ጉዲሼ በበኩላቸው ተመራቂ ተማሪዎች በትምህርት ዘመናችሁ ያጋጠሟችሁን ልዩ ልዩ መሠናክሎች ተሻግራችሁ ለዛሬው የደስታ ቀን በመብቃታቾሁ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል።
ዶክተር ኩሴ ጉድሼ ጨምረው እንደተናገሩት ተመራቂ ተማሪዎች ከፊት ለፊት የሚገጥሟቾሁን ፈተናዎች ለማለፍ አሁኑኑ ራሳችሁን በስነ ልቦና ማጠንከር ይጠበቅባቾኋል ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል።
ያነጋገርናቸው አንዳንድ ተመራቂ ተማሪዎች በበኩላቸው እንደገለፁት ከትምህርት ዓለም እርቀው ወደ አዲስ የሕይወት ምዕራፍ መሸጋገራቸው ልዩ ስሜት እንደሚፈጥርባቸው ገልፀው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ በመሣተፍ ለሃገራቸውና ለሕዝባቸው የሚጠበቅባቸውን ለማከናወን ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፡ ወንድዬ ካሳ

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ