“ምክር ቤቶቻችን ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ውይይት እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 18/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቶቻችን ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የተዘጋጀው የውይይት መድረክ ሀገራዊ ማንነት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ፋይዳን ትልቅ መሆኑን በመወያያ ሰነዱ ላይ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም የጋራ ማንነት ከመገንባት ይልቅ የግለኝነት ትርክት የሚያጎሉ ተግባራት በስፋት ይስተዋሉ ነበር።
ሀገርን በዘላቂነት ለማስቀጠል አንዱ የሌላውን መብት አክብሮ መኖርን እና ሀገራዊ ማንነት ግንባታ ላይ ማተኮር እንደሚገባም ተመላክቷል።
በውይይት መድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ: አብደላ በድሩ

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።