“ምክር ቤቶቻችን ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ውይይት እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 18/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቶቻችን ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የተዘጋጀው የውይይት መድረክ ሀገራዊ ማንነት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ፋይዳን ትልቅ መሆኑን በመወያያ ሰነዱ ላይ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም የጋራ ማንነት ከመገንባት ይልቅ የግለኝነት ትርክት የሚያጎሉ ተግባራት በስፋት ይስተዋሉ ነበር።
ሀገርን በዘላቂነት ለማስቀጠል አንዱ የሌላውን መብት አክብሮ መኖርን እና ሀገራዊ ማንነት ግንባታ ላይ ማተኮር እንደሚገባም ተመላክቷል።
በውይይት መድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ: አብደላ በድሩ

More Stories
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የምርጥ ዘር ብዜት ስራን በራስ አቅም ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ
በበልግ አዝመራ ከሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ከ70 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ