“ምክር ቤቶቻችን ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ውይይት እየተካሄደ ነው
ሀዋሳ፡ ሰኔ 18/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) ምክር ቤቶቻችን ለዘላቂ ሰላምና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የተዘጋጀው የውይይት መድረክ ሀገራዊ ማንነት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸው ፋይዳን ትልቅ መሆኑን በመወያያ ሰነዱ ላይ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም የጋራ ማንነት ከመገንባት ይልቅ የግለኝነት ትርክት የሚያጎሉ ተግባራት በስፋት ይስተዋሉ ነበር።
ሀገርን በዘላቂነት ለማስቀጠል አንዱ የሌላውን መብት አክብሮ መኖርን እና ሀገራዊ ማንነት ግንባታ ላይ ማተኮር እንደሚገባም ተመላክቷል።
በውይይት መድረኩ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ መነቴ ሙንዲኖን ጨምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
ዘጋቢ: አብደላ በድሩ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ