በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የምስራቅ ጉራጌ ዞን የልማት፣ የምስረታና የኢንቨስትመንት ፎረም በቡታጅራ ስታዲየም በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በድምቀት በመካሄድ ላይ ነው

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የምስራቅ ጉራጌ ዞን የልማት፣ የምስረታና የኢንቨስትመንት ፎረም በቡታጅራ ስታዲየም በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በድምቀት በመካሄድ ላይ ነው

በመርሐ ግብሩ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ፣ የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

በመርሃግብሩ ላይ አዲሲቷን የምስራቅ ጉራጌ ዞን በላቀ ህዝባዊ ትብብርና ተሳትፎ ለማሳደግ እንዲሁም ዞኑ ያሉትን እምቅ አቅሞችን እና ፀጋዎችን ለማስተዋወቅ ዓላማን ያደረጉ ልዩ ልዩ ሁነቶች በመካሄድ ላይ ናቸው።

ዘጋቢ፡ መሐመድ ሽሁር – ከወልቂጤ ጣቢያችን