አታላንታ ከ61 ዓመታት በኋላ ዋንጫ አነሳ
የጣሊያኑ እግር ኳስ ክለብ አታላንታ በዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ የጀርመኑን ባየር ሊቨርኩሰንን 3ለ0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ከ61 ዓመታት በኋላ ዋንጫ አንስቷል።
የአታላንታን ሶስቱንም የማሸነፊያ ጎሎች ናይጄሪያዊው አጥቂ አዴሞላ ሉክማን ሲያስቆጥር በዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ሃትሪክ የሰራ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል።
በሁሉም ውድድሮች 51 ጨዋታዎችን ሳይሸነፍ ፍፃሜ የደረሰው ባየር ሊቨርኩሰን ከ361 ቀናት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሽንፈት ደርሶበታል።
ሊጠናቀቅ ከጫፍ በደረሰው የውድድር ዘመንም የጀርመኑ እግር ኳስ ክለብ በአንድ ጨዋታ 3 ጎል ሲቆጠርበት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
አዘጋጅ፡ ሙሉቀን ባሳ
More Stories
ሀገር አቀፍ የክለቦች ሻምፒዮና ውድድር ያለምንም ችግር እንዲካሄድ በቂ ዝግጅት መደረጉን የኣሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም አታ ገለፁ
ዳራማሎ ደንዳሾ ስፖርት ክለብ ባስኬት ቡናን በማሸነፍ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና የዋንጫ አሸናፊ ሆነ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ በተደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ለፍፃሜ ያለፉ ክለቦች ተለይተው ታውቀዋል