ሀዋሳ: ሚያዝያ 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት የሰላምና ፀጥታ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::
ባለፉት ጊዜያት የክልሉን ሰላምና ፀጥታ የማስጠበቅ ሥራ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ፣ በየአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ እና የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ መድረኩ እንደሚያተኩር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገልፀዋል::
የተከናወኑ የሠላምና ፀጥታ ሥራዎችን አፈፃፀም የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እያቀረቡ ሲሆን መድረኩ የዘርፉን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል::
በመድረኩ የክልል፣ የዞንና ልዩ ወረዳ የፀጥታ መዋቅር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ