ሀዋሳ: ሚያዝያ 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት የሰላምና ፀጥታ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::
ባለፉት ጊዜያት የክልሉን ሰላምና ፀጥታ የማስጠበቅ ሥራ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ፣ በየአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ እና የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ መድረኩ እንደሚያተኩር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገልፀዋል::
የተከናወኑ የሠላምና ፀጥታ ሥራዎችን አፈፃፀም የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እያቀረቡ ሲሆን መድረኩ የዘርፉን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል::
በመድረኩ የክልል፣ የዞንና ልዩ ወረዳ የፀጥታ መዋቅር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
ህብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የምርጫ ማኒፌስቶ፣ የዕጩ ማስተዋወቂያ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ፕሮግራም በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ አካሄደ
ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጥራት ያለው የአይን ህክምና በሀገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ
ብልጽግና ፓርቲ የማህበረሰቡ ችግር የሚቀርፉ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ በማጠናቀቅ በውጤታማነት ለአገልግሎት እያበቃ ነው – ዶ/ር መሀመድ ኑርዬ