ሀዋሳ: ሚያዝያ 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት የሰላምና ፀጥታ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::
ባለፉት ጊዜያት የክልሉን ሰላምና ፀጥታ የማስጠበቅ ሥራ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ፣ በየአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ እና የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ መድረኩ እንደሚያተኩር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገልፀዋል::
የተከናወኑ የሠላምና ፀጥታ ሥራዎችን አፈፃፀም የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እያቀረቡ ሲሆን መድረኩ የዘርፉን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል::
በመድረኩ የክልል፣ የዞንና ልዩ ወረዳ የፀጥታ መዋቅር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ
More Stories
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ የልማት ዘርፍ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱን የዳዉሮ ዞን ግብርና፣ የአካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ልማት መምሪያ አስታወቀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የክልሉን አስፈፃሚ አካላት አመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ሁለተኛ ቀን ውሎ እንደቀጠለ ነው