ሀዋሳ: ሚያዝያ 29/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት የሰላምና ፀጥታ ሥራዎች አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ይገኛል::
ባለፉት ጊዜያት የክልሉን ሰላምና ፀጥታ የማስጠበቅ ሥራ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ፣ በየአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ እና የባለድርሻ አካላት ሚና ላይ መድረኩ እንደሚያተኩር ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ገልፀዋል::
የተከናወኑ የሠላምና ፀጥታ ሥራዎችን አፈፃፀም የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ እያቀረቡ ሲሆን መድረኩ የዘርፉን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችንም ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል::
በመድረኩ የክልል፣ የዞንና ልዩ ወረዳ የፀጥታ መዋቅር አካላት እየተሳተፉ ይገኛል::
ዘጋቢ፡ ማሬ ቃጦ

More Stories
በጎፋ ዞን የዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ፓርቲውን በሀብት ለማጠናከር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ
የጓሮ አትክልትና የተለያዩ ሰብሎችን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ መቻላቸውን በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የሶያሜ ቀበሌ አርሶአደሮች ተናገሩ
በከተማው በተያዘው በጀት ዓመት በ5 ወራት ውስጥ 1 ቢሊየን 5 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ አስታወቀ