የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 26/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የትንሳኤን በዓል በማስመልከት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ያለፉት የፆምና የፀሎት ጊዜያት በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ መንፈሳዊ ሕይወትን በማደስ ፈሪሃ ፈጣሪን የተላበሰ ስብዕናና ሞራላዊ እሴትን ለማጠናከር ጉልህ ሚና የተጫወቱ ናቸዉ ብለዋል።
በየእምነቶቻችን አስተምህሮዎችና ድንጋጌዎች መሠረት የምናከናዉናቸዉ ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች ዉስጣዊና ዉጫዊ ሠላምን በማጎናፀፍ የእርስበርስ ትስስራችን በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ እንዲመሠረትና እንዲጠናከር ድልድይ ሆነዉ የሚያገለግሉ ናቸዉ ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።
በፆሙ ጊዜያት ያጎለበትናቸዉ መልካም ተግባራት የአብሮነትን ድልድይ የሚያጠናክሩ፣ መልካምነትን የሚያላብሱ፣ የመተባበርና የመቻቻል ሠንሰለትን የሚያጎለብቱ በመሆናቸዉ የዘወትር የምግባርና የተግባር መርሆዎቻችን ሆነዉ እንዲቀጥሉ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
በዓሉ የሐሴት፣ የበረከትና የሠላም እንዲሆንላችሁ በድጋሚ እመኛለሁ ሲሉ ነው ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው መጥቀሳቸውን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያሳያል።

More Stories
ሀገራዊ ምክክር፤ የመደማመጥ፣ የመግባባትና የጠንካራ ሀገረ መንግሥት ግንባታ መሠረት ነው!
ከ23 ሚሊየን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ ተገለጸ
በግንቦት እና ሰኔ 2018 ዓ.ም ወራት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፣ በቱሪዝም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ፣ በዲጂታል ኢትዮጵያ፣ በሀገር በቀል ሪፎርም እና ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።