የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 26/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የትንሳኤን በዓል በማስመልከት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ያለፉት የፆምና የፀሎት ጊዜያት በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ መንፈሳዊ ሕይወትን በማደስ ፈሪሃ ፈጣሪን የተላበሰ ስብዕናና ሞራላዊ እሴትን ለማጠናከር ጉልህ ሚና የተጫወቱ ናቸዉ ብለዋል።
በየእምነቶቻችን አስተምህሮዎችና ድንጋጌዎች መሠረት የምናከናዉናቸዉ ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች ዉስጣዊና ዉጫዊ ሠላምን በማጎናፀፍ የእርስበርስ ትስስራችን በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ እንዲመሠረትና እንዲጠናከር ድልድይ ሆነዉ የሚያገለግሉ ናቸዉ ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።
በፆሙ ጊዜያት ያጎለበትናቸዉ መልካም ተግባራት የአብሮነትን ድልድይ የሚያጠናክሩ፣ መልካምነትን የሚያላብሱ፣ የመተባበርና የመቻቻል ሠንሰለትን የሚያጎለብቱ በመሆናቸዉ የዘወትር የምግባርና የተግባር መርሆዎቻችን ሆነዉ እንዲቀጥሉ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
በዓሉ የሐሴት፣ የበረከትና የሠላም እንዲሆንላችሁ በድጋሚ እመኛለሁ ሲሉ ነው ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው መጥቀሳቸውን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያሳያል።

More Stories
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ