የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የትንሳኤን በዓል በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 26/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው የትንሳኤን በዓል በማስመልከት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት ያለፉት የፆምና የፀሎት ጊዜያት በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ መንፈሳዊ ሕይወትን በማደስ ፈሪሃ ፈጣሪን የተላበሰ ስብዕናና ሞራላዊ እሴትን ለማጠናከር ጉልህ ሚና የተጫወቱ ናቸዉ ብለዋል።
በየእምነቶቻችን አስተምህሮዎችና ድንጋጌዎች መሠረት የምናከናዉናቸዉ ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች ዉስጣዊና ዉጫዊ ሠላምን በማጎናፀፍ የእርስበርስ ትስስራችን በፍቅር፣ በመከባበርና በመቻቻል ላይ እንዲመሠረትና እንዲጠናከር ድልድይ ሆነዉ የሚያገለግሉ ናቸዉ ሲሉም ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው ጠቁመዋል።
በፆሙ ጊዜያት ያጎለበትናቸዉ መልካም ተግባራት የአብሮነትን ድልድይ የሚያጠናክሩ፣ መልካምነትን የሚያላብሱ፣ የመተባበርና የመቻቻል ሠንሰለትን የሚያጎለብቱ በመሆናቸዉ የዘወትር የምግባርና የተግባር መርሆዎቻችን ሆነዉ እንዲቀጥሉ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
በዓሉ የሐሴት፣ የበረከትና የሠላም እንዲሆንላችሁ በድጋሚ እመኛለሁ ሲሉ ነው ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው መጥቀሳቸውን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያሳያል።

More Stories
የክልሉ ሕዝቦች ሰላምና አንድነት እንዲጎለብት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን የብሔረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ገለጹ
ብሔራዊ መግባባት የሰፈነባትን ሀገር ለትውልድ ለማስረከብ ሀገራዊ ምክክሩ ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑ ተገለጸ
የኮንታ ዞን ም/ቤት 4ኛ ዙር 4ኛ ሥራ ዘመን 26ኛው መደበኛ ጉባኤው ተጠናቀቀ