ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 26/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሠላምና በጤና አደረሳችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የትንሳኤ በዓል ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች ያለውን ፅኑ ፍቅር በመስቀል ላይ ያሳየበት እንዲሁም ይቅርታና ምህረትን ለሰው ልጆች የሰጠበት የጥልና የመለያየት ግድግዳን አፍርሶ የሰውን ልጅ የታደገበት በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩት መንፈሳዊ በዓላት አንዱ ነው ሲሉም ተናግረዋል በመልዕክታቸዉ።
ይህ የትንሳዔ በዓል መታዘዝን፣ይቅርታንና ምህረትን እንዲሁም አንዱ ለሌላው መተሳሰብ እንዳለበት የሚያስተምረን ሲሆን መረዳዳትንና መጠያየቅን ከተለመደው ባህል ባለፈ በፍጹም መንፈሳዊነት ስሜት በጎዳና ላይ የወደቁትን በማሰብ፣በህግ ጥላ ስር ያሉትን በመጠየቅ፣ታመዉ የተኙትን በማጽናናትና ካለን ላይ በማካፈል በአብሮነት ትንሳኤውን የምናከብርበት በዓል ሊሆን ይገባልም ስሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች በደል ተላልፎ በመሰጠት የሰውን ልጆች ከጨለማ ወደ ብርሃን ነጻ ለማውጣት ዋጋ የከፈለበት በመሆኑ እኛም አቅሜ ደካሞችን በመርዳትና ካለን በማካፈል ና ለወገኖቻችን በመድረስ ና በመተሳሰብ በዓሉን እንዲናከብር ጥሪ አቅርበዋል።
ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የትንሳኤ በዓል ለክልላችና ለሀገራችንና ህዝቦች እንዲሁን ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን የሰላም፣የበረከት፣ የመተሳሰብና የፍቅር እንዲሆንም መመኘታቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመለክታል።
More Stories
የህዝቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላትና መንግስታዊ አገልግሎቶችን በተገቢው ለመስጠት የውስጥ ገቢ ግብርን አማጦ ለመሰብሰብ በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ተገለጸ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ የልማት ዘርፍ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ መምጣቱን የዳዉሮ ዞን ግብርና፣ የአካባቢ ጥበቃና ኅብረት ሥራ ልማት መምሪያ አስታወቀ