የስቅለት በዓል በሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ገብርኤል ደብረ ምህረት ገዳም

የስቅለት በዓል በሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ገብርኤል ደብረ ምህረት ገዳም

ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 25/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የስቅለት በዓል በሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ገብርኤል ደብረ ምህረት ገዳም በጾም፣ በጸሎት እና ስግደት በእምነቱ ተከታዮች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡

የስቅለት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት እንዲሁም በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስርዓቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡

የስቅለት በዓል የኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት የሚታሰብበት ዕለት ሲሆን በእለተ አርብ ያያቸው የስቃይ፣ መከራና እንግልት ጊዜያት ስለ ፍጹም ፍቅር ሲል  እንደሆነ ይታመናል፡፡

ዘጋ፡ ብዙነሽ ዘውዱ