የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ማእድ አጋሩ
ሀዋሳ፡ ሚያዝያ 24/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ከተማ ለሚገኙ ከ300 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማዎችና አረጋዊያን ነው የትንሣኤ በአልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ ያጋሩት፡፡
የሚስተዋለውን የኑሮ ውድነትና ማሕበራዊ ችግር በመተጋገዝና በመተባበር መቅረፍ እደሚገባ የገለጹት ርእሰ መስተዳደሩ፥ ባለፋት 4ና 5 አመታት የአቅመ ደካማዎችን ማህበራዊ ኃላፊነት በመጋራት፥ ቤታቸውን በማደስና በመስራት፣ ማእድ በማጋራት መርሀ ግብር ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል፡፡
የሲዳማ ክልል ወጣቶችና ሕፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እመቤት ኢሳያስ በበኩላቸው፥ በዚህ ማእድ ማጋራ ፕሮግራም ላይ የተሳተፉ አረጋውያን አቅመ ደካማ እንዲሁም ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የተደረገ መሆኑን ጠቁመው፥ እንደ ክልል በአሉን ምክንያት በማድረግ ከ15 ሺህ በላይ ለሆኑ ድጋፍን ለሚሹ ወገኖች ተደራሽ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው አሁን ላይ ከ300 በላይ ለሚሆኑ አቅመ ደካማዎች ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚሁ ወቅት በዓሉን ለሚያከብሩ መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳቹ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ቤተልሔም ለገሰ

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ