ትንሳኤ ከሞት ወደ ህይወት መነሳትን ማሳያ ብቻ አይደለም የትህትናም መገለጫ ነው – መላከ ገነት አባ ደጉዋለ አፀደ አሰፋ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ለተከታታይ 55 ቀናት በፆም፣ በፀሎትና በስግደት እንዲሁም መልካም ተግባራት እየተናወነ የሚያልፈው ይህ ወር በተለይ የፆሙ መገባደጃ ሳምንት ለሰው ልጆች ትህትናንና ታዛዥነት በሰፊው የሚታይበት ሳምንት መሆኑን መላከ ገነት አባ ደጉዋለ ገልጸዋል፡፡
“ጌታችን በዚህ እለት የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠቡ ትህትናን፤ የይሁዳን እግር በማጠቡ ትዕግስትን ገልጧል ይኸውም አርአያነቱን ትህትናውን የገለጠ ብቻ ሳይሆን የአለምን ሀጥያት ለማጠብና ለማንፃት መምጣቱን ማሳያ ነው” በማለት ገልፀውታል፡፡
በእለተ ሐሙስ ቤተ ክርስቲያኗ ኢየሱስ ክርስቶስ በፍጹም ትህትና የሀዋሪያትን እግር በማጠብ ዝቅ ማለትን ለታናሽ መታዘዝን በሰፊው ያሳየበት ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ዕለቱ ከሰባቱ ምሥጢራት ቤተ ክርስቲያን አንዱ ምሥጢረ ቁርባን ስለመመሥረቱና ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ በማቅረቡ የሰው ልጅ ነጻነት ያገኘበት ቀንም ነው፡፡
ስርአተ ፀሎት በሰፊው የተገለፀበት መሆኑን አንስተው “በዚች እለት በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ካህናቱ ስርአቱን አድርሰው የምዕመናኑን እግር በማጠብ ከጌታችን ከመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተማርነውን ትህትናን በተግባር በማስተማር እዲሁም ምእመናኑ የተማሩትን ትህትና በተግባር በማሳየት በታላቅ ድምቀት ይከበራል” ብለዋል፡፡
“በዚች ዕለት በሰፊው የሚታየው ትህትና በየአንዳንዳችን ሕይወት ገብቶ ሰላም ትዕግስትን መተባበርን ከሁሉም በላይ ይቅርታን የምንማርበት በመሆኑ እኛም ከእየሱስ ክርስቶስ የተማርነውን በሰፊው በመግለፅ ይቅር መባባል መታገስ ራስን ዝቅ ማድረግ ትህትናን ማሳየት አለብን” በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋ፡፡
አዘጋጅ ፡ ቤተልሔም ለገሰ

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ