ኢንተር ሚላን የጣሊያን ሴሪአ ዋንጫን ለ2ዐኛ ጊዜ አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ

ኢንተር ሚላን የጣሊያን ሴሪአ ዋንጫን ለ2ዐኛ ጊዜ አሸናፊ መሆኑን አረጋገጠ

የጣሊያኑ እግር ኳስ ክለብ ኢንተር ሚላን የጣሊያን ሴሪአ ዋንጫን ለ20ኛ ጊዜ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል።

ኢንተር ሚላን አሸናፊ መሆኑን ያረጋገጠው በሚላን ደርቢ (ደርቢ ዴላ ማዶኒና) ታሪካዊ ባላንጣውን ኤሲ ሚላንን 2ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፉ ነው።

በዚህም ሴሪአው ሊጠናቀቅ 5 የጨዋታ ሳምንታት እየቀረው ከተከታዩ ኤሲ ሚላን ጋር የ17 ነጥብ ልዩነት በመፈጠሩ ኢንተር ገና ከወዲሁ አሸናፊ መሆኑ ታውቋል።

ሴሪአው በ116 ዓመታት ታሪኩ የዋንጫ አሸናፊው በደርቢ ዴላማዶኒና ሲታወቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

አዘጋጅ፡ ሙሉቀን ባሳ