የሐዘን መግለጫ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወይዘሮ አለሚቱ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሐዘን ገለፀ።
ወይዘሮ አለሚቱ በክልሉ ጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊነትን ጨምሮ በዞኑ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ለረዥም አመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህዝብን አገልግለዋል።
ወይዘሮ አለሚቱ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ የጋሞ ዞን ገረሴ ቦንኬ ምርጫ ክልል ህዝብን በመወከል፤ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆን ሲያገለግሉ ነበር፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወይዘሮ አለሚቱ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ፤ ለቤተሰባቸው ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል፡፡

More Stories
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የምርጥ ዘር ብዜት ስራን በራስ አቅም ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ
በበልግ አዝመራ ከሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ከ70 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ