የሐዘን መግለጫ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወይዘሮ አለሚቱ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሐዘን ገለፀ።
ወይዘሮ አለሚቱ በክልሉ ጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊነትን ጨምሮ በዞኑ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ለረዥም አመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህዝብን አገልግለዋል።
ወይዘሮ አለሚቱ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ የጋሞ ዞን ገረሴ ቦንኬ ምርጫ ክልል ህዝብን በመወከል፤ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆን ሲያገለግሉ ነበር፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወይዘሮ አለሚቱ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ፤ ለቤተሰባቸው ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል፡፡

More Stories
በ6 ወራት ውስጥ ሊመዘበር የነበረ ከ156 ሚሊየን 560ሺህ ብር በላይ ማዳን መቻሉ ተገለጸ
የጉራጌ ክትፎ ባህልና እውቀትን በዩኒስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ቅርስ ባለስልጣን ገለፀ
በክልሉ ያሉ ብሔረሰቦችን ባህል ወደፊት በማውጣት የአካባቢውን ሰላምና ልማት ለማስቀጠል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳደር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ተናገሩ