የሐዘን መግለጫ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወይዘሮ አለሚቱ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሐዘን ገለፀ።
ወይዘሮ አለሚቱ በክልሉ ጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊነትን ጨምሮ በዞኑ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ለረዥም አመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህዝብን አገልግለዋል።
ወይዘሮ አለሚቱ ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ የጋሞ ዞን ገረሴ ቦንኬ ምርጫ ክልል ህዝብን በመወከል፤ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆን ሲያገለግሉ ነበር፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በወይዘሮ አለሚቱ አሰፋ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ፤ ለቤተሰባቸው ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛል፡፡

More Stories
የቅድመ በሽታ መከላከል ተግባራትን በአግባቡ በመፈፀም ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የሸዋል ዒድ (ቀሊ ፍቼ) ባህላዊ ስርዓት በስልጤ
ሁሉም ሰው ዴሞክራሲያዊ መብቱን ተጠቅሞ በቀጣይ የሚያስተዳድረውን መንግስት መምረጥ እንዲችል የምርጫ ካርድ በወቅቱ መያዝ እንደሚጠበቅበት ተገለጸ