የሴቶችና ህፃናትን ጥቃት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ: ሚያዚያ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ተባለ።
የአሪ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ከፍትህ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በሴቶችና ህፃናት በሚፈፀሙ ጥቃቶች ላይ ምክክር አድርገዋል።
መድረኩን በንግግር የከፌቱት የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘረፍ ኃላፊና የዞኑ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ኢያሱ ዘርፉ በሴቶችና ህፃናት ላይ የምደርሰውን የትኛዉንም ጥቃት ለመከላከል እንዲያስችል የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ከፍትሕ አካላት ጋር በተቀናጀ ሁኔታ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ፡፡
የኣሪ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ሲስተር ርብቃ አለማየዉ እንደገለጹት የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሴቶችና ህፃናት ተጋላጭነትን በመቀነስ ተጠቃሚነትና ተሳትፏቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ዘጋቢ: ሁሴን ዓለሙ- ከጂንካ ቅርንጫፍ

More Stories
እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ሥራ ከዳር ለማድረስ በሚደረገው ርብርብ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ገለፀ
በትምህርት ሴክተር የመረጃ አያያዝ ውጤታማነት ዙሪያ በኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ
ሁሉንም የመማሪያ መጻሕፍት ባለማግኘታቸው በትምህርታቸው ላይ ጫና እየፈጠረባቸው መሆኑን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቆንጋና ቆቄ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተናገሩ