የሴቶችና ህፃናትን ጥቃት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ

የሴቶችና ህፃናትን ጥቃት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ

ሀዋሳ: ሚያዚያ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ተባለ።

የአሪ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ከፍትህ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በሴቶችና ህፃናት በሚፈፀሙ ጥቃቶች ላይ ምክክር አድርገዋል።

መድረኩን በንግግር የከፌቱት የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘረፍ ኃላፊና የዞኑ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ኢያሱ ዘርፉ በሴቶችና ህፃናት ላይ የምደርሰውን የትኛዉንም ጥቃት ለመከላከል እንዲያስችል የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ከፍትሕ አካላት ጋር በተቀናጀ ሁኔታ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ፡፡

የኣሪ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ሲስተር ርብቃ አለማየዉ እንደገለጹት የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሴቶችና ህፃናት ተጋላጭነትን በመቀነስ ተጠቃሚነትና ተሳትፏቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ዘጋቢ: ሁሴን ዓለሙ- ከጂንካ ቅርንጫፍ