የሴቶችና ህፃናትን ጥቃት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ
ሀዋሳ: ሚያዚያ 10/2016 ዓ.ም (ደሬቴድ) በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ተባለ።
የአሪ ዞን ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ከፍትህ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በሴቶችና ህፃናት በሚፈፀሙ ጥቃቶች ላይ ምክክር አድርገዋል።
መድረኩን በንግግር የከፌቱት የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘረፍ ኃላፊና የዞኑ መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ኢያሱ ዘርፉ በሴቶችና ህፃናት ላይ የምደርሰውን የትኛዉንም ጥቃት ለመከላከል እንዲያስችል የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ከፍትሕ አካላት ጋር በተቀናጀ ሁኔታ ሊሰራ ይገባል ብለዋል ፡፡
የኣሪ ዞን ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ሲስተር ርብቃ አለማየዉ እንደገለጹት የስርዓተ ፆታ እኩልነትን ለማረጋገጥ የሴቶችና ህፃናት ተጋላጭነትን በመቀነስ ተጠቃሚነትና ተሳትፏቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ዘጋቢ: ሁሴን ዓለሙ- ከጂንካ ቅርንጫፍ

More Stories
የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የምርጥ ዘር ብዜት ስራን በራስ አቅም ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምርጥ ዘር ድርጅት አስታወቀ
በበልግ አዝመራ ከሚከናወኑ የግብርና ስራዎች ከ70 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለማግኘት ታቅዷል – አቶ ማስረሻ በላቸው
የመንግሥትን የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚሰሩ የማህበረሰብ ልማት ድርጅቶች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት በተሻለ ለማረጋገጥ በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል – አምባሳደር ፍጹም አረጋ