የቤንች ሸኮ ዞን ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ እንደገለፁት በያዝነው የክረምት ወራት ከ16 ሚሊዮን 632 ሺህ በላይ የቡና ችግኞች ለመትከል ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
ቡና የዞኑ ትልቁ ኢኮኖሚና የገቢ ምንጭ በመሆኑ ለአርሶ አደር ብቻ የሚተው እንዳልሆነና በተሻሻለ የቡና ዝሪያዎች ማሳ እንዲሸፈን በማደረግ በሁሉም ወረዳዎች ከ16 ሚሊዮን በላይ ጉድጓዶች መዘጋጀቱን ኃላፊው ተናግረዋል።
የሚተከሉ የቡና ችግኞች በመንግስት ተቋማትና በልማታዊ ባለሀብቶች መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
በዞን 157 ሺህ 592 ሄክታር ማሳ በቡና በቡና የተሸፈነ መሆኑን ተናግረው ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ ከፍ ያለ ምርት የሚያስገኝ ሥራ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
ዘጋቢ፦ አብዲሳ ዮናስ- ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት (ኢጋድ) አባል ሀገራት ኘሮጀክት አስተባባሪዎች እና የግብርና ሚንስቴር ብሔራዊ ኘሮጀክት ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን የድርቅ መቋቋሚያና ዘላቂ የአርብቶ አደር ኑሮ ማሻሻያ ኘሮጀክት የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
የከተማዋን መሠረተ ልማት ለማስፋፋት በሚደረገው ሂደት የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የቀለጣ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ
ዲጂታል ኢትዮጵያን የመፍጠሪያ ጊዜን በማፋጠን ኢትዮጵያን የመጪው ዘመን መሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ተገለጸ